የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በአምራች ኢንዱስትሪው እየታየ ያለው መነቃቃት መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ድጋፍና ክትትል ውጤት ነው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን ፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦ በአምራች ኢንዱስትሪው እየታየ ያለው መነቃቃት መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ድጋፍና ክትትል ውጤት መሆኑን በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አሥተባባሪ አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

በደብረ ብርሃን ከተማ በአንድ ቢሊዮን ብር ወጪ የተገነቡ አራት አምራች ኢንዱስትሪዎች ተመርቀው ወደ ምርት ገብተዋል።


በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አሥተባባሪ አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ መንግስት ልዩ ትኩረት ከሰጣቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች አንዱ ኢንዱስትሪ ነው።


በዘርፉ ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን በመለየትና መፍትኤ በመስጠትም አሁን ላይ ተጨባጭ ውጤት መምጣቱንም ገልጸዋል።

በተለይም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለኢንዱስትሪው መነቃቃት ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም አንስተዋል።

ቀደም ባሉት ጊዜያት የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ46 በመቶ ያልበለጠ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ለዘርፉ በተሰጠው ትኩረት 64 በመቶ መድረሱን አመልክተዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ብቻም 93 በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ አንቀሳቃሾች ወደ መካከለኛ የአምራች ኢንዱስትሪ መሸጋገራቸውን ተናግረዋል።

መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪ በሰጠው ድጋፍና ክትትል በዘርፉ መነቃቃት መፍጠሩንም ተናግረዋል።


የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሃላፊ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው፣ በክልሉ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ በአማራ ክልል 85 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸው ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለተኪ ምርት ዕድገት ቁልፍ ሚና ተጫውቷል ብለዋል።

የደብረ-ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት፣ ከተማዋ ምቹ የኢንዱስትሪ መዳረሻ እንደመሆኗ በዘርፉ ለመሰማራት የሚፈልጉ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ ነው ብለዋል።


ለዚህ ደግሞ በአንድ ቢሊዮን ብር ወጪ ተገንብተው ወደ ሥራ የገቡ የዱቄት፣ የፕላስቲክና የጫማ ማምረቻ አራት ኢንዱስትሪዎች ማሳያ ናቸው ብለዋል።

በከተማዋ በበጀት ዓመቱ እስካሁን ድረስ 15 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፣ በዚህም ከ7ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026