የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኮሪደር እና መልሶ ማልማት አነስተኛ ቢዝነሶችን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ለስራ እና ለሸማቹ ሳቢ በሆነ መንገድ መልሶ በመገንባት የተሰራ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና መልሶ ማልማት ስራ አነስተኛ ቢዝነሶችን የሚያዳክም ሳይሆን፣ ይበልጥ ዘመናዊ፣ ለስራ እና ለሸማቹ ሳቢ በሆነ መንገድ መልሶ በመገንባት የተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በአጠቃላይ እስከ አሁን በተሰራው 5 ሺህ 490 ያህል አዳዲስ ንግድ ሱቆችን የተገነቡ እና ነባሮቹንም ከመንገድ setback ወደ ኋላ በመሳብ እንደገና በአዲስ መልክ እንዲገነቡ መደረጉን ጠቅሰዋል።


ከእነዚህም ውስጥ 2 ሺህ 800 ያህሉ እንደ አዲስ የተገነቡ፣ ቀሪዎቹ 2 ሺህ 690 ደግሞ ከመንገድ setback ወደ ኋላ በመሳብ እንደገና በአዲስ መልክ ደረጃቸውን በማሻሻል የተገነቡ ናቸው ብለዋል።

ከዚህ ውስጥ 55 በመቶ የሚሆነው ግንባታ በባለቤቶቹ መገንባታቸውን ገልጸው፤ ቀሪውን በቀበሌ እና በቤቶች ኮርፖሬሽን ውስጥ ሲነግዱ ለነበሩ መንግስት ገንብቶ ለልማት ተነሺዎች ያስረከባቸው መሆናቸውን አስታውቀዋል።

እንዲሁም መሬት ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆኑት ደግሞ በአክሲዮን ተደራጅተው እንዲገነቡ እያደረግን ነው ብለዋል።


በመሆኑም ከተማዋ ለንግድ ስራ ቀላል፣ ይበልጥ ሳቢና ምቹ መደረጓን ጠቅሰው፤ የቢዝነስ እንቅስቃሴው እንዲዳከም አለመደረጉንም ገልጸዋል።

ከንቲባዋ በመልዕክታቸው ልክ በሌሎቹ ኮሪደሮች እንዳደረግነው ሁሉ ትላንት ማምሻውን በይፋ ክፍት የተደረገው የድል ፕላዛ እና የቁርጡሚ ወንዝ ዳርቻ የልማት ተነሺዎችን አስተናግደንበታል ብለዋል።


ቀደም ሲል ከቦሌ አትላስ እስከ ብራስ መንገድ በኮሪደር ልማቱ ምክንያት ተነስተው የነበሩ የንግድ ተቋማት፣ አሁን በዚሁ ፕላዛ ውስጥ ስራቸውን በስኬት ጀምረዋል ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026