የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተከናወኑ ተግባራት ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅም አድጓል

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ኢንቨስትመንትን ምቹ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅም ማደጉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ሶማሌ ክልሎች የዘርፉ የስራ ሀላፊዎች ገለጹ።

መንግሥት ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኢኮኖሚ ሪፎርም በማድረግ ኢትዮጵያን ለኢንቨስትመንት ምቹ የሚያደርጉ ተግባራትን አከናውኗል።

የኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥ ማሻሻያ፣ ዲጂታል አሰራርን ማስፋት፣ የህግ ማዕቀፎችን ማሻሻል እና ለንግድ ስራው ማነቆ የሆኑ የአሰራር ስርዓት ሰንሰለቶች ርዝመትን የሚቀርፉ በርካታ ሪፎርሞች ተደርገዋል።

ለኢንቨስተሮች የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና መሰረተ ልማትን በሚገባ ለማሟላት የተከናወኑ ተግባራት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳራሻ እያደረጋት ይገኛል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አባስ መሀመድ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ተግባራዊ የተደረገው የኢኮኖሚ ሪፎርም ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው።

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ 146 ባለኃብቶች በተለያዩ መስኮች ለመሰማራት መሬት መውሰዳቸውንና ኢንቨስት ለማድረግ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

ወደ ክልሉ የሚመጣው የኢንቨስትመንት ፍሰት እየጨመረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ውጤት ነው ብለዋል።

በክልሉ ኢንቨስትመንትን የሚያበረታቱ አሰራሮች እየተተገበሩ መሆኑን ጠቁመው፤ መሬትን ባነሰ የሊዝ ዋጋ ማቅረብን ጨምሮ ክልሉ ለኢንቨስትመንት ያለውን እምቅ አቅም በሰፊው የማስተዋወቅ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለኢንቨስትመንቱ በተፈጠረው ምቹ ምህዳር የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይም ተጨባጭ ውጤቶች እንዲገኝ አስችሏል ነው ያሉት።

የሶማሌ ክልል የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር አህመድ ረሺድ በበኩላቸው፤ በክልሉ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በሆቴልና ቱሪዝምን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት በምግብ ማቀነባበር፣ በግብርና፣ በእንስሳት መኖ አቅርቦት፣ ሪል ስቴትን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ባለኃብቶች ኢንቨስት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ከለውጡ በኋላ በክልሉ የሰፈነው ሠላም እንዲሁም ኢንቨስትመንት ምቹ ማድረግ ላይ የተሰሩ ሥራዎች ውጤት ማምጣታቸውንም አብራርተዋል።

በዚህም በክልሉ ለባለኃብቶች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በተለያዩ መስኮች እንዲሰማሩ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል።

በክልሉ ኢንቨስት የሚያደርጉ ባለኃብቶች ከፋይናንስ፣ ከመሰረተ ልማት አቅርቦት እና ሌሎች አገልግሎቶች የሚገጥማቸውን ችግሮች ለመፍታት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ክልሉ በኢንቨስትመንት በኩል ያሉትን አቅሞች አሟጦ ለመጠቀም የሚያደርገው ጥረት በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026