የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማነቃቃት ተግባራዊ ያደረጋቸው ሁለንተናዊ የሪፎርም ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ነው

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማነቃቃት ተግባራዊ ያደረጋቸው ሁለንተናዊ የሪፎርም ስራዎች ተጨባጭና ተስፋ ሰጪ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

በ4ኛ 'ኢንቨስት በኢትዮጵያ' ፎረም ''ኢትዮጵያ ለቢዝነስ ዝግጁ ናት" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።


ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ያላትን ዝግጁነት በተግባር እያረጋገጠች መሆኑን ተጠቁሟል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት በኢንቨስትመንት መስክ እውነተኛ ሽግግር ላይ ትገኛለች።

የዘንድሮው ፎረም መሪ ሃሳብም የፍላጎት መግለጫ ሳይሆን፣ በተግባር የታየ እድገትን፣ ግልጽ አሰራርንና ቀልጣፋ አገልግሎትን የሚያንጸባርቅ መሆኑን አስረድተዋል።

አሁን ላይ ትልቁ ለውጥ የታየው አቅምን ከማስተዋወቅ ባለፈ ውጤትን ወደ ማሳየት፣ ከውይይት ደግሞ ወደ ተግባር መሸጋገራችን ነው ብለዋል።

ለዚህም እንደ ማሳያ ባለፈው ዓመት የተካሄደውን "በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ" ፎረምን ከ58 ሀገራት የተወጡ ከ750 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚገመት የኢንቨስትመንት ቃል ኪዳን መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡

መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲነቃቃና ተመራጭነቱ እንዲጨምር ያከናወናቸው የሪፎርም ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተለይም በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አማካኝነት በማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ በህግ ማዕቀፎችና በተቋማዊ አሰራሮች ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎች ለዘርፉ መጠናከር ትልቅ መሰረት መጣላቸውን ተናግረዋል፡፡

ወደ ትግበራ የገቡ በርካታ ኩባንያዎች በአሁኑ ወቅት ምርቶቻቸውን ለዓለም አቀፍ ገበያ ማቅረብ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

ይህም ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ፍላጎቶችን ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር አቅሟን እያጠናከረች መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ሪፎርሙ የታሰበውን ግብ እንዲመታና የሀገሪቱ ብልፅግና እንዲረጋገጥ ሁሉም የባለድርሻ አካላት ርብርባቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026