🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጠንካራ የዕድገት አፈጻጸም እንዲመዘገብ ማስቻሉን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ።
የገንዘብ ሚኒስቴር በ18 ወራት የተከናወኑ የማክሮ ኢኮኖሚ እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ውጤታማነት የሚገመግም ዝርዝር ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በሀገሪቱ ተግባራዊ የተደረገው ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ እያደረገ ይገኛል።
የሀገሪቱ አጠቃላይ ምርት ተከታታይነት ያለው ዕድገት እያሳየ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ኢትዮጵያን በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ካላቸው ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ አስችሏታል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ዘርፉ የኢኮኖሚው ሞተር ሆኖ መቀጠሉን ጠቅሰው፤ የግብርና እና የአገልግሎት ዘርፎች የላቀ አፈጻጸም እያሳዩ መሆኑን ጠቁመዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃው ካመጣቸው ትልቁ ድሎች አንዱ ላለፉት ዓመታት ፈታኝ ሆኖ የቆየውን የዋጋ ግሽበት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ መቻሉ መሆኑን ገልጸዋል።
የተቀናጀ የፊስካልና የገንዘብ ፖሊሲ ተግባራዊ መደረጉ የኑሮ ውድነቱን ጫና በማቃለል ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤት ማስመዝገቡን አብራርተዋል።
የምንዛሬ ተመን ማሻሻያውን ተከትሎ በሀገሪቱ የወጪ ንግድ ላይ ታሪካዊ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም ገበያ ያላቸው ተወዳዳሪነት በመጨመሩና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ ማደጉን ጠቅሰው፤ ከዚህ በተጨማሪ የሐዋላ ገቢ፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ፍሰትና የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ የታየው መሻሻል ከፍተኛ ነው ብለዋል።
መንግሥት የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን በማዘመኑ ጠቅላላ ገቢው ከፍ እንዲል ማድረጉን ጠቅሰው፤ ይህም የሀገሪቱን የውጭ ዕዳ ጫና በዘላቂነት ለመቀነስ እየተደረገ ያለውን ጥረት በእጅጉ ማገዙን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ የኢኮኖሚ ማሻሻያ በተቀናጀ አመራርና በማስረጃ ላይ በተደገፈ ትንታኔ እየተመራ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይም መዋቅራዊ ለውጦችን በማጠናከር የተረጋጋና እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚ ለመገንባት በቁርጠኝነት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026