የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምዕራብ ሸዋ ዞን ለ2018/19 የምርት ዘመን የግብርና ግብዓቶች እየቀረቡ ነው

Apr 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የ2018/19 ምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ የማቅረብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ የኅብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ አስታወቀ።

የኤጀንሲው ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በምርት ዘመኑ የታቀደውን የሰብል ልማት ግብ ለማሳካት የተለያዩ የግብርና ግብዓቶች ከወዲሁ ለአርሶ አደሩ እየተሰራጩ ይገኛሉ።


በምርት ዘመኑ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማሰራጨት ታቅዶ እየተሠራ ሲሆን፤ እስካሁን ከ461 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ በየወረዳው ለሚገኙ መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማህበራት ደርሷል ብለዋል።

የማዳበሪያ አቅርቦቱ ለአርሶ አደሩ በዲጂታል አገልግሎት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይኸም ለፍትሐዊ ስርጭቱ እንደሚያግዝ አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ 8 ሺህ 244 ኩንታል ምርጥ ዘር ለማሰራጨት ታቅዶ፣ እስካሁን ከ2 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር ቀርቧል ነው ያሉት።

ይህ የግብዓት ስርጭት በዋናነት በአምቦ እና በቦረባኮ የገበሬዎች ዩኒየን በኩል እየተከናወነ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ ግብዓቶችም በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል።

ይህ ዝግጅት በዞኑ በመስኖና በመኸር የሚካሄደውን የሰብል ምርታማነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑንም አክለዋል።

አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የኢኮኖሚ አቅሙን እንዲያሳድግና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ተስማሚ የሆኑ ሰብሎችን እንዲያመርት አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ወይዘሮ መሰረት ገልጸዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የዞኑ አርሶ አደሮች ግብዓቶቹ በወቅቱ መድረሳቸው ለሥራቸው መሳካት ትልቅ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።


አርሶ አደር ሀጫሉ ባይሳ፤ "በመጪው መኸር በቆሎና ሌሎች ሰብሎችን ለማልማት የሚያስፈልገንን ግብዓት አግኝተናል፤ አሁን ላይ መሬታችንን ደጋግመን በማረስ ለዘር ዝግጁ እያደረግን ነው" ብለዋል።

ሌላው አርሶ አደር ወልደሰማያት ለታ፤ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በወቅቱ መድረሱ የእርሻ ሥራቸውን በጊዜ ለማቀላጠፍ እንደረዳቸው ጠቅሰው፣ በአምስት ሄክታር መሬታቸው ላይ በቆሎና ጥራጥሬ ለማልማት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።


ከዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በ2018/19 ምርት ዘመን በምዕራብ ሸዋ ዞን ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ይለማል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026