🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፡- ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር ሁሉ በጣም ወሳኝ እና የኢኮኖሚ ልብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም፤የመደመር መንግሥት መጽሐፍ በፖለቲካና በኢኮኖሚ መካከል ሚዛን መጠበቅ፣ ፖለቲካል ኢኮኖሚን በትክክል መግራትና መረዳት አስፈላጊ ነው ብሎ በሚዛን የሚነሳ መሆኑን አስረድተዋል።
አንዱ ገዝፎ አንደኛው ያነሰ እንደሆነ፤ የሚፈለገውን ሥር ነቀል ለውጥ ማምጣት ያስቸግራል ሲሉም አመላክተዋል።
ለዚህ ነው የመደመር መንግሥት ሚዛን ጠብቆ ድርሻቸው ሳይዛባ አንዱ ለአንደኛው መከታ ተሸካሚ ሆኖ በጋራ ብልጽግናን ማረጋገጥ እንዲችሉ በትኩረት የተሠራው ብለዋል።
ይህ እንዳለ ሆኖ የብዙ መንግሥታት የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ኢንዱስትሪ ለመለወጥ (ለማደግ) ለሚያስብ ሀገር ሁሉ በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል።
አክለውም፤ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026