የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው ሲሉ የአውሮፓ ሕብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ ገለጹ።

የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም "ዓለም አቀፍ የገበያ መግቢያ አቅምን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

የአውሮፓ ሕብረት ዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መስራች፣ የቡና መገኛ፣ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነች ታሪካዊ ሀገር ናት።


ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ መዳረሻዋ የት እንደሆነ በግልጽ አሳይታለች ብለዋል።

የአውሮፓ ሕብረት ደረጃቸውን የጠበቁ የመሰረት ልማትና የዲጂታል መሰረተ ልማት ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ሕብረቱ በገጠር መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ ቢዝነስ ፎረም በንግድ ድርጅቶች መካከል፣ በመንግሥት እና በንግድ ድርጅቶች መካከል ገንቢ ውይይት ማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጣ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረጓንም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

ዛሬ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ከበጀት ድጋፍ ስምምነቱ ባሻገር የ150 ሚሊዮን ዩሮ የዲጂታል ኢኮኖሚ ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል፡፡

ይህም በዲጂታል መሰረተ ልማት፣ ክህሎትና አስተዳደር በጋራ ማዕቀፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑን አብራርተዋል።


የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ዋና ጸሀፊ ዋምኬሌ ሜኔ፤ አፍሪካ ከአራት ሺህ በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በመሳተፍ በዓለም ቀዳሚዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህ ትብብር በአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ የተበጣጠሰ የእሴት ሰንሰለት ባለው የዓለም ገበያ በአፍሪካ የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል።

ኢትዮጵያ የቢዝነስ ስራዎችን የሚያቀላጥፉ የጉምሩክና የፋይናንስ ስርዓቷን እያዘመነች መሆኑን ጠቅሰው፤ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት መፈጠሩን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ትርጉም ያለው ሪፎርም በማድረግ ሀገሪቷን በአፍሪካ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት አድርጓታል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ቁልፍ የፋይናንስ ተቋማትን አቅም በማጠናከር የተሳለጠ የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026