🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ ላይ የህዝብ ይፋዊ ውይይት አድርጓል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጀ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ረቂቅ አዋጁ ሀገራዊ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እንዲሁም ከዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ድንጋጌዎች ጋር የተናበበ ለማድረግና የጉምሩክን አሰራር ለማዘመን የተደረገ ማሻሻያ ነው።
የጉምሩክ አሰራር ላይ እንቅፋት የፈጠሩ ድንጋጌዎችን በማሻሻል በወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።

ዘርፉን በማዘመን የጉምሩክ ስርዓቱ ዓለም ከደረሰበት የአሰራር ስርዓት ጋር የበለጠ እንዲጣጣም ያስችላል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ፤ ማሻሻያው አስፈላጊ እና በትክክለኛ ጊዜ የተደረገ ነው ብለዋል።

በረቂቅ አዋጁ የተካተቱት ማሻሻያዎች ኮንትሮባንድን እና ህገ ወጥ ንግድን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እንደሚያግዝ ገልፀዋል።
ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያስችልም ተናግረዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ሁኔታ ውስጥ ጠንካራ የጉምሩክ ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ማሻሻያው ምቹ የንግድ እንቅስቃሴን ለመፍጠርና የንግድ ሥርዓቱ ሚዛኑን ጠብቆ እንዲካሄድ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የህግ ባለሙያ አቶ አብርሃም ረጋ በበኩላቸው፤ አዋጁን ማሻሻል ያስፈለገበት ምክንያት ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ከደረሰበት የእድገት ደረጃ ጋር ለማጣጣም እና ለሀገር ወስጥ ኢንዱስትሪ ከለላ ለመስጠት እንደሆነ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ህገ ወጥ ንግድ መከላከል፣ የድንበር ጥበቃ፣ ከዓለም አቀፍ የንግድ ስምምነት ጋር ለማጣጣም፣ ድንበርን ለመጠበቅ፣ የስታቲስቲክስ መረጃን ለመያዝ እንዲሁም ሕጋዊ ንግድንና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እንደሆነም ገልጸዋል።
በአዋጁ ላይ 22 የሚሆኑ አንቀፆች ማሻሻያ እንደተደረገባቸው በዚሁ ጊዜ አስታውቀዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026