የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከማዕድን ዘርፍ ወጪ ንግድ አራት ቢሊዮን ዶላር ገደማ ገቢ ተገኝቷል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከማዕድን ዘርፍ ኤክስፖርት አራት ቢሊዮን ዶላር ገደማ ገቢ መገኘቱን የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ገለጹ፡፡

የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ በሰጡት ማብራሪያ፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከማዕድን ወጪ ንግድ ወደ አራት ቢሊዮን ዶላር ገደማ ገቢ መገኘቱን ይፋ አድርገዋል።

እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፣ በዘርፉ የታየው ውጤት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ87 በመቶ እድገት አሳይቷል።

ይህ የአራት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ከሦስት ዓመታት በፊት የሀገሪቱ አጠቃላይ ዓመታዊ የኤክስፖርት ገቢ የነበረውን ያህል መሆኑ፣ ዘርፉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ያመጣውን ግዙፍ ለውጥ ያመላክታል ብለዋል።

ለዘርፉ ስኬት ዋነኛው ምክንያት የሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተለይም ባለሀብቶች ያገኙትን ትርፍ በውጭ ምንዛሬ ወደ ውጭ ማውጣት መቻላቸው፤ የኢንቨስትመንት ስጋቶች መቀነሳቸው እና መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ልዩ የማበረታቻ ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ ግዙፍ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ አድርጓል ነው ያሉት።

ከወርቅ ባለፈ ሌሎች ማዕድናትም ትኩረት እንደተሰጣቸው አንስተዋል።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የወርቅ ሀብት ካላቸው ሀገራት ተርታ እየተሰለፈች ሲሆን፥ ከወርቅ በተጨማሪ ሌሎች ማዕድናት ላይ ትኩረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

እስካሁን በፍለጋ ደረጃ የነበሩ እንደ ጋዝ፣ ፖታሽ፣ ሊቲየም እና ኒኬል ያሉ ማዕድናት ወደ ምርት እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ነው ያነሱት።

እነዚህ ማዕድናት በቀጣይ የዘርፉን የኤክስፖርት ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳድጉትም አንስተዋል።

ከማዕድን ወጪ ንግድ ባሻገር እንደ ብረት፣ ሲሚንቶ እና ድንጋይ ከሰል ያሉ ማዕድናት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን በማሟላት የውጭ ምንዛሬን ለማዳን ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ ነው ያሉት።

ከሀገር ውስጥ ፍላጎት የሚተርፈው ምርት ደግሞ ወደ ውጭ ገበያ እንደሚላክ አስረድተዋል።

አዲስ የተረቀቀው የማዕድን ፖሊሲ ሲጸድቅ እና አሁን የተጀመረው የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ ሲቀጥል፣ ዘርፉ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ይበልጥ እንደሚያድግ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026