የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማላመድ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል 

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማላመድ የግብርና ምርታማነትን ማረጋገጥ መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የይርጋጨፌ ግብርና ምርምር ማዕከል ግንባታ ማስጀመሪያ የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሃ ግብር ተካሄዷል።

ማዕከሉ ለጌዴኦ፣ ለቡርጂ፣ ለኮሬ ዞኖች የግብርና ምርምር በተለይም የቡና እና የእንሰት ምርታማነትን ለማሻሻል ትኩረት ተደርጎ እንደሚገነባም ተመላክቷል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በክልሉ ምርምርን መሠረተ ያደረገ የግብርና ልማትን በማረጋገጥ የአርሶ አደሩን ችግር ለማስወገድ እየተሠራ ነው።


በተለይ ቴክኖሎጂን በማፍለቅ፣ በማላመድና አዳዲስ የምርምር ሙከራዎችን በማከናወን ረገድ በርካታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።

የቡና ዝርያ ለማሻሻልና አሰራርን ለማዘመን በተደረገ ጥረት በሞዴል አርሶ አደሮች ማሳ በሄክታር እስከ 20 ኩንታል የቡና ምርት ለማምረት መቻሉን ለአብነት ጠቅሰው ይህንን ማስፋት ዋናው የማዕከሉ ተልዕኮ ነው ብለዋል።

በተያዘው ዓመት ብቻ በሰብልና እንስሳት ጨምሮ በአምስት የግብርና ምርምር ዘርፎች 39 ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጉን ያነሱት ደግሞ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አብዮት መብራቴ (ዶ/ር) ናቸው።


የምርምር መሠረተ ልማትን በማስፋትና የተመራማሪዎችን ቁጥር በማሳደግ የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተው የይርጋጨፌ የግብርና ምርምር ማዕከልም የዚሁ አካል ነው ብለዋል።

ማዕከሉ ለጌዴኦ፣ ለቡርጂና ለኮሬ ዞኖች በግብርና ምርምር በተለይም የቡና እና የእንሰት ምርታማነትን ለማሻሻል ትኩረት አድርጎ እንደሚሠራም ተናግረዋል።

ይህም በክልሉ ሶስት ብቻ የነበሩትን የምርምር ማዕከላት የይርጋጨፌን እና የሳውላ ምርምር ማዕከላትን በመጨመር ወደ አምስት የሚያሳድግ ነው ብለዋል።

የይርጋጨፌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ በበኩላቸው ፤በወረዳው ከ16 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት የተሸፈነ መሆኑን ገልፀዋል።


በወረዳው የቡናን ተፈጥሯዊ ጣዕም ጠብቆ ምርታማነቱን ለማሳደግ በተደረገ ጥረት በሞዴል አርሶ አደሮች ማሳ በሄክታር እየተገኘ ያለውን የከፍተኛ ምርት ተሞክሮ ለማስፋት የምርምር ማዕከሉ መገንባቱ ድርሻው የጎላ መሆኑንም አመልክተዋል።

የማዕከሉን ግንባታ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት እንደሚሰሩ ያረጋገጡት ደግሞ የክልሉ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አረጋ በዴቻ ናቸው።


ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ የተመደበለት ማዕከሉ የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ በሚቀጥሉት ስድስት ወራት የሚጠናቀቅ ሲሆን የአስተዳደር ህንጻ፣ ቤተሙከራ፣ የምርምር ማካሄጃ ስፍራዎችና መሰብሰቢያ አዳራሾችን ያካተተ መሆኑም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026