🔇Unmute
ጅማ ፤ ሚያዝያ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት እድገትና ማንሰራራት የሚደነቅ መሆኑን በካናዳ ዮርክ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁር አሊ አስጋሪ (ፕ/ር) ተናገሩ።
ኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥ እውን ለማድረግ እየተጋች መሆኑ ይታወቃል።
ከዲጂታል ልማትና የቴክኖሎጂ እድገት በተጓዳኝ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሀይል በብዛት የማፍራት ስራ እየተከናወነም ይገኛል።
በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ዜጎችን በነፃ ተጠቃሚ የሚያደርገው የ5 ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠናም የዚሁ ጥረት ማሳያ ነው ።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ ላለው የዲጂታል ልማት በተለይም ደግሞ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን እና ፈጠራን ለማስፋፋት የሚደረገው ጥረት በላቀ ውጤት እየተገለጠ እና የበርካቶችን እውቅና እያገኘ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው መሾማቸውም የጥረቱ ስኬት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ።
በጅማ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ ላይ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም በተመለከተ ተሞክሯቸውን ለማካፈል ከተገኙት በካናዳ ዮርክ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁር አሊ አስጋሪ (ፕ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት እድገትና ማንሰራራት ለሌሎች ሀገራት በጥሩ በተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማትና ተግባራዊ እንቅስቃሴዋ አስደናቂ መሆኑን በማንሳት በአጭር ጊዜ የመጣው ውጤት እና የታየው ስኬት ለቀጣይም ትልቅ ተስፋ የሰነቀ ሆኗል ብለዋል።
ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ልማት በተጓዳኝ በዘርፉ ብቁ የሰው ሃይል ለማፍራት የሚደረገው የተቀናጀ ጥረትም የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል።
በኢትዮጵያም የተቋማት ግንባታና የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ትልቅ ትርጉም የሚኖረው መሆኑን አንስተው ለዚህም ጠንካራ መሰረት እያኖረች መሆኑን ተመልክቻለሁ ብለዋል።
ከዩኒቨርሲቲ ምሁራንና ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር በነበራቸው ውይይት የተረዱትም ይህንኑ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ በዘርፉ ልማትና ትግበራ ትልቅ ተስፋ የሰነቀችና ወደፊት እየተራመደች ያለች ሀገር መሆኗን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል ብለዋል።
ኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም እየሰራች መሆኑ ደግሞ በቀጣይ ለዘርፉ ልማት ሌላ እመርታ የሚያመጣ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት የያዘችውን ተግባራዊ እቅድ እያሳካች የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂክ ትግበራን በስኬት አጠናቅቃ ሌላ የዲጂታል 2030 ስትራቴጂክ እቅድ ነድፋ በመተግበር ላይ መሆኗ ይታወቃል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026