የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በቤተሰብ ደረጃ በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን እውን እያደረጉ ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡-በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በቤተሰብ ደረጃ በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን እውን እያደረጉ መሆኑን የሲዳማ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ ገለጹ።

"ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር የተዘጋጀ የውይይት መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሄዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ፤ በክልሉ አዳዲስ የግብርና ኢንሼቲቮች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ ብለዋል።


በተለይም በሰብል ልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በእንስሳት ሀብት ልማት በስፋት ስለመሰራቱ አንስተዋል።

በመሆኑም በክልሉ በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በቤተሰብ ደረጃ በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን እውን እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሸን ኮሚሽነር ወገኔ ብዙነህ፤ እንደ ሀገር የተያዙ በምግብ ራስን የመቻል ግቦችን በመከተል በክልሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እና ውጤትም እየተገኘባቸው ነው ብለዋል።


በዚህም ከጥቂት ዓመት በፊት እህል ሲሰፈርላቸው የነበሩ በርካታ አርሶ አደሮች ከችግርና ድህነት የወጡ መሆኑን አንስተው በክልሉ የተጀመሩ የግብርና ልማት ኢንሼቲቮች በስፋት የሚቀጥሉ መሆኑን ተናግረዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ለማ መሰለ (ዶ/ር)፤ በበኩላቸው በክልሉ ለአደጋ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም የመገንባት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።


የክልሉን ልዩ ፀጋና አቅም በመለየት በተሰሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ለሀገር የተረፉ የግብርና ምርቶች እየተመረቱ ይገኛሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026