የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከተማው በለውጡ ዓመታት የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳ ውኃ፤ ግንቦት11/2018 (ኢዜአ)--በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃ ከተማ በለውጡ ዓመታት የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን የዞኑ መስተዳድር አስታወቀ።

የዞኑ መስተዳድር የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ በዞኑ በለውጡ ዓመታት የህዝቡን መሰረታዊ ፍላጎቶች መሰረት ያደረጉ በርካታ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።

​"በገንዳ ውኃ ከተማም ሆነ እንደዞን የተገነቡና አሁንም በግንባታ ላይ ያሉ የልማት ሥራዎች የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ የጤና፣ የትምህርት፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድና ሌሎች የመሰረተ ልማት ሥራዎች እንደሚጠቀሱም ተናግረዋል።

በቀጣይም በተገባው ቃል መሰረት ተጨማሪ የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት የአካባቢውን እድገት አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።

​በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የአስተዳደር ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጥላሁን መኳንንት በበኩላቸው፤ በከተማዋ እየታዩ ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው።

​በአካባቢው ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን የተከናወኑ የልማት ሥራዎች በቀጣይ ዘላቂ ሰላምን በመገንባት ህዝቡን ከዚህም በላይ ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚቻል ማሳያ ናቸው ብለዋል።

የተጀመሩ የተቋማት ግንባታ ሥራዎች በፍጥነትና በጥራት እንዲጠናቀቁ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉም አረጋግጠዋል።

​የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪ አቶ አስቻለው ጋሻው በበኩላቸው ቀደም ሲል በከተማዋ የነበሩ የመሰረተ ልማት እጥረቶች በለውጡ ዓመታት በተሰሩ ሥራዎች ከፍተኛ መሻሻል መታየቱን ገልጸዋል።

​በተለይም የአካባቢውን ሀብት በጥሬ እቃነት የሚጠቀም የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካ ግንባታ ለአልሚ አርሶ አደሮችና ለሥራ ፈላጊ ወጣቶች ከፍተኛ ጥቅም የሰጠ መሆኑን አብራርተዋል።

"የአካባቢያችን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ ልማቱ እንዲፋጠንና ተጠቃሚነታችን እንዲያድግ የበኩላችንን እንወጣለን" ብለዋል።

በእለቱ የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካ፣ አዲስ የተገነቡ ትምህርት ቤት እና ጤና ጣቢያ፣ ሆቴል፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ የአሚኮ ምዕራብ ጎንደር ቅርንጫፍ ግንባታና ሌሎች ተቋማት ተጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026