የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በካፋ ዞን የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት አሳድገዋል

May 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦በካፋ ዞን ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደጋቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በካፋ ዞን ሺሾእንዴ ወረዳ ከ44 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል።

ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል ሞዴል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት፣ የወሺ ፏፏቴ የቱሪስት መዳረሻ፣ ሞዴል ጤና ኬላ እንዲሁም የኖባ ሽመሮ እና ወሺ ጊዳ የመንገድ መሰረተ ልማት ይጠቀሳሉ።


የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ እንደገለፁት፤ በዞኑ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት አሳድገዋል።

ዛሬ የተመረቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶችም የዚሁ ማሳያዎች ናቸው ያሉት አቶ እንዳሻው፣ በዞኑ በዚህ ዓመት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመቅረፍ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በትምህርቱ ዘርፍ የሚስተዋለውን የጥራትና ውጤታማነት ችግር ለመፍታትም ሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።


የጤና አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረግ ትኩረት የተሰጠው አንዱ ተግባር ነው ያሉት አስተዳዳሪው በዚህም የጤና ተቋማትን ከመገንባት ባለፈ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተሰራው ስራ ውጤት ማስመዝገቡን ነው የተናገሩት፡፡

የቱሪስት መዳረሻን በማልማት ረገድ ለወጣቶች ስራ ዕድል በመፍጠርና ቱሪስቶችን ለመሳብ በተደረገው ጥረት ዛሬ የተመረቀው የወሺ ፏፏቴ መዳረሻም የተደበቀውን እምቅ ሀብት አጉልቶ ያወጣ ነው ብለዋል።

የሺሾእንዴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደምሴ ገብረማርያም በበኩላቸው፣ በወረዳው የህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለሆኑ የመንገድ፣ የትምህርት፣ የጤናና ሌሎች መሰረተ ልማት ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።


በዛሬው እለት የተመረቁት መንገዶች አርሶ አደሩ ምርቱን ለገበያ እንዲያወጣ እንዲሁም በፍጥነት የጤና አገልግሎትን እንዲያገኝ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው ነው ብለዋል፡፡

የወረዳው ነዋሪዎችም ከዚህ ቀደም በአካባቢያቸው መንገድ ባለመኖሩ ምርታቸውን ወደ ገበያ ለማውጣትም ሆነ ወደ ጤና ተቋማት ፈጥኖ ለመድረስ ይቸገሩ እንደነበር ተናግረዋል።


ዛሬ የተመረቁት የትምህርት፣ የመንገድና የጤና ተቋማት ለበርካታ ዓመታት ይነሱ የነበሩ ጥያቄዎችን የመለሱ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026