🔇Unmute
ነጌሌ ቦረና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው የመኸር እርሻ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ከ339 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት ለማልማት ሥራ መጀመሩን የምዕራብ ጉጂ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።
ዞኑ በአምስት ዋና ዋና ሰብሎች በሚያከናውነው በዚህ የመኸር አዝመራ ከ8 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ማቀዱን የጽሕፈት ቤቱ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ ታሪኩ ብዙአየሁ ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት በዘጠኝ ወረዳዎች 339 ሺህ ሔክታር እንደሚለማና በልማት ሥራውም ከ293 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች እተሳተፉ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል።
እስካሁን ባለው እንቅስቃሴም በሁሉም የዞኑ ወረዳዎች የመጀመሪያ ዙር የእርሻ ሥራ መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።
በመኸር አዝመራው በስፋት ስንዴ፣ ጤፍ፣ በቆሎ፣ ቦለቄና ማሾ እንደሚለማ ገልጸው፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የተለያዩ ስልቶች ተግባራዊ ይደረጋሉ ብለዋል።
ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ በበቂ ሁኔታ እንዲቀርብ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ የግብርና ሥራውም በትራክተር፣ በመስመርና በኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026