የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምዕራብ ጉጂ ዞን በመኸር እርሻ ከ339 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት ይለማል

May 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነጌሌ ቦረና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው የመኸር እርሻ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ከ339 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት ለማልማት ሥራ መጀመሩን የምዕራብ ጉጂ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።


ዞኑ በአምስት ዋና ዋና ሰብሎች በሚያከናውነው በዚህ የመኸር አዝመራ ከ8 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ማቀዱን የጽሕፈት ቤቱ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ ታሪኩ ብዙአየሁ ገልጸዋል።


በዚህም መሠረት በዘጠኝ ወረዳዎች 339 ሺህ ሔክታር እንደሚለማና በልማት ሥራውም ከ293 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች እተሳተፉ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል።


እስካሁን ባለው እንቅስቃሴም በሁሉም የዞኑ ወረዳዎች የመጀመሪያ ዙር የእርሻ ሥራ መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።


በመኸር አዝመራው በስፋት ስንዴ፣ ጤፍ፣ በቆሎ፣ ቦለቄና ማሾ እንደሚለማ ገልጸው፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የተለያዩ ስልቶች ተግባራዊ ይደረጋሉ ብለዋል።


ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ በበቂ ሁኔታ እንዲቀርብ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ የግብርና ሥራውም በትራክተር፣ በመስመርና በኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026