የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

Jun 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው 43ኛውን ዓመታዊ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ግምገማ ጉባዔ ’’ለአካባቢ ተስማሚ ፈጠራና ስነ ምህዳር ጥበቃ ለጽኑ ማህበረሰብ ግንባታ’’ በሚል መሪ ሀሳብ እያካሄደ ነው።

የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ዩስፍ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው በግብርና፣ በጤና፣ በቴክኖሎጂ፣ በትምህርት፣ በህግ፣ በህብረተሰብ ሳይንስና በሌሎችም የምርምር ተግባራት እያከናወነ ነው።


በተለይም ዘንድሮ ዩኒቨርሲቲው 116 ፕሮጀክቶች ላይ የምርምር ስራ እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥም 42ቱ መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከ1 ቢሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ የሚያከናውናቸው የጥናትና ምርምር ቴክኖሎጂዎችም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ እንደሚገኙም አስታውቀዋል።

ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮ ዓመትም ከ95 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ማሰራጨቱን አመልክተዋል።

በዩኒቨርሲቲው ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና አስተዳደር ጋር በተያያዘ በድሬዳዋ አስተዳደር፣ በሐረማያ ሀይቅ፣ በአዴሌ፣ ደንጋጎ እና ሌሎች ተፋሰስ አካባቢዎች ላይ የተቀናጀ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በማህበረሰብ አገልግሎትና ተሳትፎ በኩልም ከ150ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ነፃ የህግ አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎች ዘርፎች አመርቂ ተግባራት ማከናወኑን አንስተዋል።

የግምገማ መድረኩ ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን አበረታች ስራዎች ለማስቀጠልና የሚስተዋሉ ውስንነቶች ለመቅረፍ እንደሚያስችል ተመላክቷል።

ዩኒቨርሲቲው ለ43ኛ ጊዜ በሚያካሂደው የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ጉባዔ 32 የምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል።

ለሶስት ቀናት በተሰናዳው በዚሁ ጉባዔ ላይ የዩኒቨርሲቲው ምሁራንና ተመራማሪዎች፣ ሴክተር መስሪያ ቤቶች፣ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የማህበረሰብ ተወካዮች፣ አባ ገዳዎችና ሃደ ሲንቄዎች እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026