የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ ሳምንቱን ሙሉ ምርት የሚያቀርቡ የግብይት ማዕከላትን በማቋቋም ለማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርት እየቀረበ ነው 

Jun 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ ለማቅረብ በተቋቋሙ የግብይት ማእከላት ከእሁድ እስከ እሁድ ምርቶች እየቀረቡ እንደሚገኝ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለፀ።

የቢሮው ምክትልና የግብይት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደስታ ዶሌቦ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በክልሉ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርቶችን በግብይት ማዕከላት በስፋት የማቅረብ ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል።

በዚህም በክልሉ ከ140 በላይ ከእሁድ እስከ እሁድ ምርት የሚቀርብባቸው የግብይት ማዕከላትን በማቋቋም ለማህበረሰቡ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።



ቢሮው በክልሉ 5 ከተሞች ዘመናዊ የግብይት ማዕከላት ማስገንባቱንና የወራቤ ከተማ ዘመናዊ የግብይት ማዕከል ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን አስታውሰዋል።

የግብይት ማዕከሉ አምራችና ሸማቹን ማህበረሰብ በቀጥታ በማገናኘት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ማስቻሉን ገልጸዋል።

የስልጤ ዞን ነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ሽታ መሀመድ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም የሚያመርቱትን ምርት በቀላሉ ለማህበረሰቡ ለማቅረብ የሚያስችል የግብይት ማዕከል ባለመኖሩ ገበያ ወዳለበት ስፍራ ይጓዙ እንደነበር ተናግረዋል።



በወራቤ ከተማ ተገንብቶ የተጠናቀቀው ዘመናዊ የግብይት ማዕከል የሚያመርቱትን ምርት ለማህበረሰቡ በቀላሉ ለማቅረብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

በከተማው ስራ የጀመረው የግብይት ማዕከል የሚፈልጉትን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስቻለ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወራቤ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ሳድያ ጀማል ናቸው።



በከተማው ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው ዘመናዊ የግብይት ማዕከል ምርትን በጥራትና በፈለጉት ጊዜ ለማግኘት ማስቻሉን ተናግረዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በቅርቡ በወራቤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትንና ዘመናዊ የግብይት ማዕከልን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026