የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የተገልጋይ እንግልትን ለማስቀረት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት ተግባራዊ ሆኗል

Jun 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ):- በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋለውን ሕገወጥነትና የተገልጋይ እንግልት ለማስቀረት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ መደረጉን የኦሮሚያ ክልል ትራንስፖርት ኤጀንሲ አስታወቀ።


ኤጀንሲው አዲስ ተግባራዊ ባደረገው ‘ኦሮ ዲጂታል ቲኬት’ አገልግሎት እና ዘርፉን ለማዘመን እየተከናወኑ ባሉ የሪፎርም ሥራዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል።


የኤጀንሲው ኃላፊ ከማል ማሜ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ምቹ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ ‘ኦሮ ዲጂታል ቲኬት አገልግሎት’ ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል።


ዘመናዊ አሠራሩ በዘርፉ ሲስተዋል የነበረን ብልሹ አሠራር፣ የመልካም አሥተዳደር እጦትና የተጋልጋዮችን እንግልት በመከላከል ተጨባጭ ውጤታ እያመጣ መሆኑንም አመላክተዋል።


በመናኸሪያና በአካባቢው የሚስተዋሉ ሕገወጥ ተግባራትን ለማስቀረት የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ማኅበራትና የቦርድ አመራሮች ያለቸው ሚና የጎላ መሆኑንም አስገንዝበዋል።


በአሁኑ ወቅት ከ17 ሺህ በላይ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ዲጂታል ሲስተሙ መግባታቸውን የገለጹት ደግሞ በኤጀንሲው የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ዳይሬክተር ሙስባሁዲን አብዱልመጂድ ናቸው።


በቴክኖሎጂ የተደገፈው አሠራር በስምሪት ላይ ያሉ ተሽከርካሪዎችን ለመለየት፣ ከመናኸሪያ ውጪ የሚጭኑ ተሽከርካሪዎች ተከታትሎ ለመቅጣት፣ ያለአግባብ የስምሪት መውጫ መስጠት ችግርን ለማስቅረት እና አገልግሎት አሰጣጡን ከወረቀት ንክኪ ነፃ ለማድረግ የጎላ ጥቅም እንዳለውም አስረድተዋል።


የኦሮሚያ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ማኅበራት የቦርድ ሰብሳቢ ታምራት በየነ በበኩላቸው፤ ኤጀንሲው የጀመረው የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን የማዘመን ሥራ የተሽከርካሪ አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣምና አገልግሎቱን ለማቀላጠፍ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026