የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለሃብቶች በገበያ ማረጋጋት ሂደት አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ አግዟል 

Jun 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተደረገላቸው ድጋፍ ምርታማነታቸውን በማሳደግ በገበያ ማረጋጋት ሂደት ላይ አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ባለሃብቶች ገለጹ።

በአማራ ክልል ከ414 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱንም የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታውቋል።

በባህር ዳር ከተማ "የአለማየሁ ሀይማኖት ዘይት ፋብሪካ" ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ እሱባለው ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለሚነሱ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለማግኘት አግዟል።

በንቅናቄው የነበረባቸው ችግር መፈታቱ ምርታማነታቸው እንዲያድግና ገበያ በማረጋጋት ሂደት የድርሻቸውን እንዲወጡ ማስቻሉን ገልጸዋል።

ባገኙት ድጋፍ የዘይት ፋብሪካው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ወደማምረት ሥራ መግባቱን የተናገሩት አቶ ሀብታሙ፣ በቀን ከ20 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት በማምረት ለህብረተሰቡ እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሌላው በኮምቦልቻ ከተማ የ"ይመር አሊ ዱቄትና ብስኩት ፋብሪካ" ተወካይ አቶ ደረጀ ገብሬ በበኩላቸው፣ መንግስት ለኢንቨስትመንት ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የፋብሪካው ምርታማነት እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

"በተለይ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተደረገልን ድጋፍ ተኪና ለወጪ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን ማምረት እንድንችል አድርጎናል" ያሉት ባለሃብቱ፣ ፋብሪካው ከውጭ ይገባ የነበረን የብስኩት ምርት በሀገር ውስጥ በማምረት መተካቱን ገልጸዋል።

የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተፈሪ ታረቀኝ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲነቃቃ ማድረጉን ገልጸዋል።

ለዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ 414 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 3 ሺህ 518 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን በማሳያነት አስረድተዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል።

ችግሮች በቅንጅት እንዲፈቱ፣ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታማነት እንዲጨምር፣ ገበያውን እንዲያረጋጉና ተጠቃሚ እንዲሆኑም ማስቻሉን ተናግረዋል።

በቀጣይም የኤሌክትሪክ ኃይል እና የመሬት አቅርቦትን ጨምሮ የዘርፉን ማነቆዎች በመፍታት በኢንዱስትሪው ዘርፍ ከፍተኛ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መድረክ ትናንት በኮምቦልቻ ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026