🔇Unmute
ወልድያ፤ ሰኔ 5/2018(ኢዜአ)፦ በወልድያ ከተማ የተመለከትነው የልማት ውጤት በችግር ውስጥም ሆኖ ህዝብን የሚጠቅምና ለእድገት መሰረት የሚሆን ስኬት ማስመዝገብ እንደሚቻል ተሞክሮ ያገኘንበት ነው ሲሉ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ከንቲባዎች ገለጹ።
የአማራ ክልል የ40 ከተሞች አስተዳደር ከንቲባዎችና የከተማና መሰረት ልማት ስራ አስኪያጆች በወልድያ ከተማ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ማምሻውን ጎብኝተዋል።
የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት፣ የተከናወነው ልማት ለወልድያ ከተማ አዲስ ፋና የፈነጠቀ ነው።

በጉብኝታችን የኮሪደር፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና ሌሎች የልማት ስራዎች በአጭር ጊዜና በጥራት ተጠናቅቀው ለአገልግሎት የበቁ መሆናቸውን ተገንዝበናል ብለዋል።
ይህም የአመራር ቁርጠኝነቱ ካለ በችግር ውስጥም ተሁኖ አስደማሚ የልማት ስራዎችን በማከናወን ህዝብን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚቻል ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል።
የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሸሪፍ ቃሲም በበኩላቸው የወልድያ ከተማ በፍጥነት ተለውጣ መመልከቴ ግርምትን ፈጥሮብኛል ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የከተማውን ገጽታ በመቀየር አዲስ ውበት ከማጎናጸፋቸው ባለፈ ትልቅ ልምድ የምንቀስምበት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

አመራሩ ከህብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ የሰራው ልማት የወልዲያ ከተማን ገጽታ በመቀየር አመርቂ ውጤት አስገኝቷል ያሉት ደግሞ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት ናቸው።
የልማት ስራዎቹ በጥራትና በፍጥነት የተገነቡ በመሆናቸው በችግር ውስጥም ሆኖ ውጤታማ ልማት ማከናወን እንደሚቻል ተምረንበታል ብለዋል።
በጉብኝቱ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር) እንዲሁም ሌሎች የክልልና የከተማ አስተዳደር አመራሮች ተሳትፈዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026