የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የወልድያ ከተማ የልማት ስኬት ለሌሎች ከተሞች በጥሩ ማሳያነት የሚጠቀስ የልማት ትጋትና ቁርጠኝነት ማሳያ ነው

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልድያ፤ ሰኔ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የወልድያ ከተማ የልማት ስኬት ለሌሎች ከተሞችም በጥሩ ማሳያነት የሚጠቀስ የልማት ትጋትና ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

የአማራ ክልል ከተማና መሰረት ልማት ቢሮ ክልላዊ የኮሪደር ልማት የልምድ ልውውጥ እና የግምገማ መድረክ በወልድያ ከተማ እያካሄደ ነው።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በክልሉ ከተሞችን በማልማት፣ በማስዋብና በማሳመር ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ ነው።

በዚህም በኮሪደር ልማትና በሌሎችም ልማቶች ተስፋ ሰጭ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፣ ህብረተሰቡም ተጠቃሚ እየሆነ ነው ብለዋል።

በተለይ የወልድያ ከተማ ችግሮችን ተቋቁማ አስደናቂ ልማት ማከናወን መቻሏ ለሌሎች ከተሞች የልምድና የተሞክሮ ማዕከል መሆን ችላለች ብለዋል።

የከተማዋ የልማት ስኬት ለሌሎች ከተሞችም በጥሩ ማሳያነት የሚጠቀስ የልማት ትጋትና ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከከተማዋ አስተዳደር የልማት ቁጭት በመማር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ላይ አተኩሮ መስራት ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።

የዛሬው መድረክም የተሻለ የሰሩ ከተሞች ልምዳቸውን በማካፈል ሌሎች እንዲማሩና እንዲነቃቁ ማስቻል ነው ብለዋል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው ከህብረተሰቡ ጋር የከተማውን ሰላም በመጠበቅ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልማቶችን ማከናወን ተችሏል ብለዋል።

በተለይም ከተማዋ በሚፈለገው ልክ አለመልማቷ የፈጠረብን ቁጭት፣ አልህና ጽናት በተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ አስችሎናል ብለዋል።

ወልድያ አሁን እየተሞሸረች፣ የእየደመቀችና ለሁሉም ምቹ እየሆነች ትቀጥላለች ሲሉም አመላክተዋል ።

ለተሞክሮ የሚሆን ተጨባጭ ውጤት ብናስመዘግብም ገና ስለሚቀረን ልማቱን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

በመድረኩ በአማራ ክልል የ40 ከተሞች ከንቲባዎች እና የመሰረት ልማት ሥራ አስኪያጆችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026