🔇Unmute
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ የማር ምርት እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በጽህፈት ቤቱ የንብና ሐር ልማት ባለሙያ የሆኑት ብርሃኑ ለችሳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዞኑ የንብ ማነብ ዘርፉን ለማዘመን በየደረጃው በተደረገው ሰፊ ጥረት የማር ምርቱን ማሳደግ ተችሏል።
በተለይም በዞኑ በሚገኙ 23 ወረዳዎች በተካሄደው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ፣ በርካታ ወጣቶች በዘርፉ ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የማር ምርቱን ይበልጥ ለማሳደግ ለአርሶ አደሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከመስጠት ባለፈ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች መሰራጨታቸውን ጠቁመው ባለሀብቶችም በዘርፉ እንዲሰማሩ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።

ይህም በዘርፉ ለተሰማሩ 200 ሺህ አርሶ አደሮች ተጨማሪ ገቢ ከመፍጠሩ በላይ፣ ህብረተሰቡ ጥራቱን የጠበቀ ምርት በገበያ ላይ እንዲያገኝ አስችሏል ብለዋል።
በ2018 በጀት ዓመት 10 ሺህ 340 ቶን ማር ለማምረት ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ ባለፉት 11 ወራት ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ማሳካት ተችሏል ነው ያሉት።
ይህ ምርት የተሰበሰበው ከ851 ሺህ በላይ ከሚሆኑ ባህላዊ፣ የሽግግርና ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች መሆኑን ጠቅሰው፣ የተገኘው የማር ምርት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ220 ቶን ዕድገት አሳይቷል ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026