🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ፤ ሰኔ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር ከትራንስፖርትም ባለፈ ለንግድና ኢንቨስትመንት ትልቅ እንደሚሆን በኢትዮጵያ አየር መንገድ የክልል ኤርፖርቶች ፋሲሊቲ ኃላፊ ተወልደ ግርማይ ገለጹ።
አየር መንገዱ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ የሚያደርገውን የቅድመ ምረቃ በረራ በዛሬው እለት ጀምሯል።

ኃላፊው ለኢዜአ እንደገለጹት የደብረ ማርቆስና አካባቢው ህብረተሰብ የቆየ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጥያቄ በመንግስት በተሰጠው ትኩረት ምላሽ አግኝቷል።
በዛሬው እለትም የቅድመ ምረቃ በረራ መጀመሩን ተናግረው በተለያዩ አካባቢዎች የዜጎችን የመሰረተ ልማትና የአገልግሎት ፍላጎት የማሳለጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

አውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት መጀመሩ ለአካባቢው ከትራንስፖርትም ባሻገር ለንግድና ኢንቨትስመንት እንዲሁም ለቱሪዝም ሴክተሩ ትልቅ አቅም መሆኑን ተናግረዋል።
የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ስለሺ ተመስገን፤ የደብረ ማርቆስና አካባቢው ህብረተሰብ የአየር ትራንስፖርት የረዥም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ በማግኘቱ ትልቅ ደስታ የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
የትራንስፖርት አገልግሎት መጀመሩም የከተማውንና የአካባቢውን የኢንቨስተመንት፣ የንግድና የቱሪዝም እንቅስቃሴ ለማፋጠን የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።
የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኑርልኝ ብርሃኑ በበኩላቸው የአየር ትራንስፖርቱ ለዘመናት የነበረውን ፍትሃዊ የልማት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
በበረራው ከተሳተፉት መካከል አቶ ባየ ገሰሰ እና ወይዘሮ ቃልኪዳን በረከት አየር መንገዱ በረራ በመጀመሩ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
የአካባቢውን ህዝብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ መሰረት አድርጎ መንግስት ፈጣን ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱም እናመሰግናለን ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026