የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፡- መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቋማትን አገልግሎት በማዘመን ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ገለፁ።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል።


አገልግሎቱ ዘመናዊ፣ፈጣን እና ቀልጣፋ መሆኑ የተገልጋዩን እንግልት ከማስቀረቱ ባሻገር ተጠያቂነትን የሚያሰፍን መሆኑንም አስረድተዋል።

በተጨማሪም በተለያዩ መስኮች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ሰፊ እድል የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።


የወልድያ ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የቴክኖሎጅ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ምስጋናው ወርቅዬ በበኩላቸው፣ በማዕከሉ 13 የከተማ አስተዳደሩና የፌዴራል ተቋማት 102 አገልግሎቶችን እየተሰጡ ይገኛሉ ብለዋል።

ተቋማቱ በቴክኖሎጂ በመታገዝ በቅንጅት አገልግሎት በመስጠታቸውም ተገልጋዩ ህብረተሰብ በአንድ ቦታ እና በአጭር ጊዜ በመስተናገዱ እርካታን እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።


በማዕከሉ የሁሉ አገልግሎት ባለሙያ አቶ ጥላሁን አስቻለሁ በበኩላቸው፣ ወደ ማዕከሉ የሚመጡ ተገልጋዮች አስቀድሞ መረጃ በመስጠት በቀላሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል።

አገልግሎቱን በማግኝት ላይ የነበሩት የወልድያ ከተማ ነዋሪ ያልጋ ጌታሁን እንዳሉት፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ስራ መጀመሩ ከእንግልትና ከአላስፈላጊ ወጭ አድኖናል ነው የሚሉት።


ቀደም ሲል ጉዳዮቻችን ለማስፈፀም የሚኬድባቸው ቦታዎች አድካሚና ረጅም ጊዜ የሚወስዱ ከመሆኑም በላይ ለእንግልት የሚዳርጉ እንደነበርም አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት ግን በማእከሉ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንደቻሉ ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026