የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ117 ሺህ በላይ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል- መምሪያው

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን ባለፉት 11 ወራት ከ117 ሺህ በላይ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ስራና ክህሎት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ፀሐይ ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የተቻለው የአካባቢውን ጸጋ በጥናት በመለየትና አልምቶ ለመጠቀም በተደረገ ጥረት ነው።

በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ከ 131 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር የታቀደ ሲሆን ባለፉት 11 ወራት 117 ሺህ 427 የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

የተፈጠረው የስራ እድል በማዕድን ልማት ፣ በኮንስትራክሽን ፣ በግብርና ፣ በአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች መስኮች መሆኑን ነው የጠቆሙት ።

በዚሁ ወቅት የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ተከታትለው የተመረቁ መሆናቸውንም አንስተዋል።


የስራ እድል ለተፈጠረላቸው ዜጎች 491 ሚሊየን ብር በላይ ብድር፣ ከ270 በላይ የመስሪያ ሼድና ኮንቴነሮች ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም በገጠርና በከተማ በግብርና ዘርፎች ስራ ለተፈጠረላቸው ዜጎች ከ15 ሺህ ሄክታር በላይ የእርሻ መሬት በመስጠት ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን አብራርተዋል።

በዞኑ የባሶሊበን ወረዳ የጁቤ ከተማ ነዋሪ ወጣት ቀለምወርቅ ገነት ፤ ከሶስት ጓደኞቹ በመደራጀት ወደ ግብርና ስራ ገብቶ ተጠቃሚ መሆን መጀመሩን ነው የሚናገረው ።

የተፈጠረለት የስራ እድል ከቤተሰብ ጥገኝነት በማውጣት ገቢ ለማግኝት ከማስቻሉ ባሻገር ሀብት ለማፍራት እንዳስቻለው ነው ያመለከተው።

የአዋበል ወረዳ የሉማሜ ከተማ ነዋሪ ወጣት ጌትነት ይመር በበኩሉ፤በዘንድሮው ዓመት ከአምስት ጓደኞቹ ጋር በመደራጀት በኮንስትራክሽን ዘርፍ የብሉኬት ምርት ላይ መሰማራቱን ነው የሚናገረው።

በመንግስት በተመቻቸላቸው የመስሪያ ቦታን ጨምሮ የ500 ሺህ ብር ብድርና ሌሎች ድጋፎች በመነሳት ወደ ስራ ተሰማርተው ገቢ ማግኝት መጀመራቸውን ነው የሚናገረው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026