🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ምርጥ የአየር ጭነት አጓጓዥ አየር መንገድ ሽልማትን አሸንፏል።
አየር መንገዱ ሽልማቱን ያገኘው የኢትዮጵያ ካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በ2026ቱ የእስያ ጭነት፣ ሎጂስቲክስ እና አቅርቦት ሰንሰለት የሽልማት ስነ ስርዓት ላይ ነው።
በዚህም የአፍሪካ ምርጥ የአየር ጭነት አጓጓዥ አየር መንገድ በመባል ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን በጠበቁ መሰረተ ልማቶች፣ ስልታዊ ጥምረቶች፣እንዲሁም አዳዲስ የሎጂስቲክስ አሰራሮች በመታገዝ ዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ እና የንግድ ግንኙነቶችን በማጠናከር ላይ እንደሚገኝም ገልጿል።
አየር መንገዱ የካርጎ ሽልማቱን ያገኘው በዘርፉ ባለድርሻ አካላትና በደንበኞች በተሰጠ ከፍተኛ ድምፅ መሆኑን አመልክቷል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህ ስኬት ዕውን እንዲሆን ላስቻሉ አጋሮች፣ደንበኞች እንዲሁም ሰራተኞች ምስጋና አቅርቧል፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026