የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በኦሮሚያ ክልል ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ሰፊ የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።

በኦሮሚያ ክልል ከ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ የቻሉ 1 ሺህ 195 የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ወደ ላቀ የኢንቨስትመንት ደረጃ የማሸጋገር ፕሮግራም በአዳማ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የጨፌ ኦሮሚያ የከተማ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አብዱልቃድር ሁሴን እንደገለጹት፤ ኢንተርፕራይዞቹ ከመንግሥት የተሰጣቸውን ዘርፈ-ብዙ ድጋፎችና ምቹ ፓኬጆችን በአግባቡ ወደ ተግባር በመቀየር ለዚህ ስኬትና የሽግግር ደረጃ በቅተዋል።


የክልሉ መንግሥት ድህነትን ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም የስራ አጥነት ችግርን በዘላቂነት ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች ባስመዘገቧቸው ስኬቶች ሳይዘናጉ፣ ይበልጥ ለላቀ ውጤት ለመብቃት በሚሰማሩበት የኢንቨስትመንት መስክ ላይ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸውም አቶ አብዱልቃድር አስገንዝበዋል።

የኦሮሚያ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በበኩላቸው፤ ኢንተርፕራይዞቹ በተሰማሩባቸው የሥራ መስኮች ውጤታማ በመሆን ወደ ኢንቨስትመንት ደረጃ መሻገራቸውን ገልጸዋል።


በተጨማሪም በመጠናቀቅ ላይ ባለው የበጀት ዓመት ብቻ ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አዲስ የሥራ ዕድል ማመቻቸት መቻሉን ኃላፊው ይፋ አድርገዋል።

ኃላፊው አክለውም፤ ወደ ሥራ ለገቡ ዜጎች ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት መሰራጨቱንና ከ10 ሺህ በላይ የሊዝ ማሽነሪዎችም ለኢንተርፕራይዞቹ መሰጠታቸውን ጠቅሰዋል።


ለሥራ አጥ ዜጎች ከተፈጠሩት የሥራ ዕድሎች መካከል የጎጆ ኢንዱስትሪ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ንግድ፣ ግብርና፣ አገልግሎት፣ ግንባታ እንዲሁም የብረታ ብረትና የእንጨት ሥራ በዋናነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በበጀት ዓመቱ ከ200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የክልሉ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ማመቻቸት መቻሉን ገልጸዋል።

ወደ ሥራ ለገቡ ዜጎች የመሥሪያና መሸጫ ቦታዎች እንዲሁም ማዕከላት መተላለፋቸውን የገለጹት ኢንጂነር ኤባ፤ በዚህም ድህነትን በመቀነስ ረገድ ወሳኝ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።


የአዳማ ከተማ ምክትል ከንቲባ ማቲያስ ሰቦቃ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በከተማዋ ሥራ አጥነትን ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በአዳማ በጎጆ ኢንዱስትሪ፣ በከተማ ግብርና በተለይም በዶሮ እርባታ፣ በወተት ላሞች ማድለብና በሰብል ልማት ዘርፎች ለሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026