የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የሸገር ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ 37 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰብስቧል

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሸገር፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):- የሸገር ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ 37 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የከተማው የገቢዎች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የሸገር ከተማ አስተዳደር በኦሮሚያ ክልል ልዩ ልዩ ወረዳዎችንና ከተሞችን በማጣመር በቅርብ ዓመታት የተመሰረተ ሰፊና አዲስ ከተማ ነው።

ከተማው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ግዙፍ የኮሪደር ልማት፣ የመሰረተ ልማት ዝርጋታና የከተማ ውበት ፕሮጀክቶችን በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።

እነዚህን ሰፊ የልማት ፍላጎቶች በራስ አቅም ለመደገፍና የከተማውን ሁለንተናዊ እድገት ለማፋጠን የውስጥ ገቢ አቅምን ማሳደግ ቀዳሚው የቤት ስራ ሆኖ ቆይቷል።

ጽሕፈት ቤቱ በበጀት ዓመቱ የሰበሰበው ይህ ከፍተኛ ገቢ፥ የከተማዋን የልማት ፕሮጀክቶች በራስ አቅም ለመሸፈንና የህዝብን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እየተደረገ ላለው ጥረት ትልቅ ስኬት እንደሆነ ይታመናል።

የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መልካሙ አምባው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 39 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ነበር።

በበጀት ዓመቱም ከተለያዩ የገቢ ምንጮች 37 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ የዕቅዱን 95 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

የገቢ አሰባሰብ ሂደቱ ስኬታማ የሆነው የታክስ አሰባሰብ ሥርዓትን ማሻሻልና ለዘርፉ ልዩ ትኩረት መሰጠቱ እንዲሁም ለግብር ከፋዮች ቀጣይነት ያለው ግንዛቤ መፍጠር በመቻሉ ነው ብለዋል።

ከዚህም ባለፈ ሕጋዊ ደረሰኝ የመቁረጥ ልምድን ማሳደግ፣ ቴክኖሎጂን በማስፋት ግብር ከፋዮች ግብራቸውን ግልጽና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲከፍሉ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት ከ400 በላይ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው በዲጂታል መንገድ የሚጠበቅባቸውን ግብር እና ክፍያዎች መፈጸም መቻላቸውን ገልጸዋል።

ይህንን የዲጂታላይዜሽን ሥርዓት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግና ወደ ሙሉ ሥራ ለማስገባት ለባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን ኃላፊው አብራርተዋል።

የዘርፉን አዋጆችና መመሪያዎች በመከተል እንደ ታክስ ስወራ ያሉ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠር የተቀናጀ ኮሚቴ ተዋቅሮ ክትትል እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

ሕገ-ወጥነትን ለመከላከል በተሰሩ ሥራዎችም በበጀት ዓመቱ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ ስድስት ነጋዴዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ መወሰዱን አስታውሰዋል።

በተጨማሪም ሕጋዊ ደረሰኝ ባለመቁረጣቸው ምክንያት በ240 ነጋዴዎች ላይ የገንዘብና አስተዳደራዊ ቅጣት መጣሉን ገልጸው፤ በቀጣይም የዲጂታል አሠራርን በማዘመንና በደንበኞች ዘንድ ግንዛቤ በመፍጠር ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሠራ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026