የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በግብርናው ዘርፍ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮች መዘርጋታቸው ከተረጂነት ለመውጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛል 

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-ባለፉት ዓመታት በግብርናው ዘርፍ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮች መዘርጋታቸው ከተረጂነት ለመውጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ ያግዘዋል ሲሉ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ።

ምሁራኑ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂና ግብዓት በወቅቱ የተሟላለት የግብርና ስራ ምርታማ በመሆኑም የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ ከተረጂነት ለመውጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት ያፋጥናል።

በጅማ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ምጣኔ ባለሙያ እና ተመራማሪ አደባ ገመቹ (ዶ/ር)፤ ግብርናው በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ምርታማነትን እያሳደገ መጥቷል ብለዋል።


ባለፉት ዓመታት መንግሥት በሁሉም እንቅስቃሴዎቹ የባለሙያዎችን እና የአርሶ አደሩን ግንዛቤ ለማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱንም አስታውሰዋል።

በዲጂታል ግብርና ትግበራ አርሶ አደሩ መሬት ለማዘጋጀትና ዘር ለመዝራት መጠቀም ያለበትን ትክክለኛ ጊዜን ጨምሮ፣ ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን እንዲያገኝ መደረጉ የምርታማነት ዕድገት ጥረቱን ወደ ተጨባጭ ውጤት እየቀየረው መሆኑን ገልጸዋል።

ለአርሶ አደሮች የምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በበቂ ሁኔታ እንዲደርስ መደረጉም ለተገኘው ውጤት ሌላኛው ምክንያት መሆኑን አክለው ገልጸዋል።

በዚህም ግብርናውን ከዝናብ ጠባቂነት በማላቀቅ በመስኖና በሌሎች አማራጮች በዓመት ሁለትና ከዚያ በላይ ማልማት፣ የአርሶ አደሩን ሕይወት ከማሻሻል ባለፈ ከተረጂነት ለመውጣት እንደሚቻል አስረድተዋል።

ከዚህ ባለፈም የገበያ ትስስርን በመፍጠር፤ የኮንትራት እርሻን ጨምሮ ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም በቀጥታ ከአርሶ አደሩ ምርት የሚረከቡ ተቋማትና ፋብሪካዎች መፈጠራቸው በዘርፉ ትልቅ ለውጥ ማምጣቱን ጠቅሰዋል።

በዩኒቨርሲቲው የግብርናና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ ዲን፣ የአፈር ልማት፣ የሰብል እንክብካቤና ንጥረ-ነገር ባለሙያ ሰለሞን ቱሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት ለግብርናው ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት ምርታማነትን በማላቅ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል።


በዚህም የፍራፍሬና የቅባት እህሎች በስፋት ከመመረታቸውም በላይ ምርቶቹን የሚያቀነባብሩ ፋብሪካዎች መቋቋማቸውን ጠቁመዋል።

በቴክኖሎጂ በመታገዝ ምርትን በአግባቡ መሰብሰብ በመቻሉም የብክነት መጠን ቀንሶ ምርታማነት መጨመር መቻሉንም አክለዋል።

እንዲሁም መንግሥት ዘመናዊ የግብዓት ማቆያና ማከማቻ ሥፍራዎችን አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረጉና ሰፊ ግንዛቤ መፍጠሩ በዘርፉ የታየ ሌላኛው ትልቅ የለውጥ ምዕራፍ መሆኑንም አስረድተዋል።

ከዚህም ባሻገር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥ ከሚያስከትለው ችግር በመከላከል ረገድ ለግብርናው ዘርፍ በጎ ሁኔታ መፍጠሩንም አመልክተዋል።

ወጣቶችን በግብርና በማሳተፍ፣ የአፈር ጥበቃ ሥራዎችን በማጎልበትና የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሳለጥ ረገድ የተሰጠው ልዩ ትኩረት ለስኬቱ አጋዥ መሆኑንም አብራርተዋል።

መሰል ሥራዎች ከተረጂነት ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት እያገዙ መሆናቸውን ጠቁመው የሚፈለገው ግብ ላይ ለመድረስ ሁላችንም ልንረባረብ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026