የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን የቅርስ ሃብቶች በዘላቂነት በመጠበቅና በማልማት ለትውልድ የሚሻገር አስደናቂ ሥራ ሰርቷል

Jul 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን የታሪክ፣ የተፈጥሮና ባህላዊ የቅርስ ሃብቶች በዘላቂነት በመጠበቅና በማልማት ለትውልድ የሚሻገር አስደናቂ ሥራ መስራቱን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ።

ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለምአቀፍ ተቋማት መሪዎች ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ጉብኝት አድርገዋል።


የዲፕሎማቲክ ልዑካን የላሊበላ ጉብኝት የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዕምቅ አቅም ለዓለም ለማስተዋወቅና በቅርስ ጥበቃ የሚደረገውን ዓለምአቀፍ ድጋፍ ለማጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የአስደናቂ ኃይማኖታዊ፣ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊና ባህላዊ ቅርሶች ባለቤት ናት።

በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት(ዩኒስኮ) የተመዘገበው የላሊባላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የኪነ-ሕንፃ የአሰራር ጥበብ ዓለምን ያስደመመ ድንቅ የጥበብ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

የላሊበላን ቅርስም ለኃይማኖታዊ ሥርዓትና ዓለምአቀፍ ጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ከፈረንሳይ መንግሥት ጋር የዘላቂ ቅርስ ጥበቃ መሠረተ ልማት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኪነ-ሕንፃ ጥበብ ከመጠበቅ ባሻገርም የአብያተ ክርስቲያናቱን የካበቱና ውድ የሥነ-ጽሑፍ ሃብቶች ዲጂታላይዝ በማድረግ ለተተኪ ትውልድ ለማስተላለፍ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ባህላዊ ሃብቶች ለመጠበቅ፣ ለመንከባከብና ለማልማት የሰጡት ትኩረት የቅርስ ጥበቃ ውጤታማነትን አሳድጓል ብለዋል።

የጎንደር አፄ ፋሲለደስ አብያተ መንግሥታት፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና የጅማ አባጅፋር ቤተ-መንግሥት ዕድሳት የመደመር መንግሥት ድንቅ ሥራ አብነቶች መሆናቸውን አስረድተዋል።


የዘላቂ ቅርስ በኢትዮጵያ ፕሮጀክት ኃላፊ ኪዳነማርያም ወልደ ጊዮርጊስ በበኩላቸው፣ በላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት ቅርስ ጥበቃ ፕሮጀክት ሥር ሰፋፊ መሠረተ ልማትቶች መካተታቸውን አረጋግጠዋል።

የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የቅርስ ጥበቃ ፕሮጀክትም ቅርሱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትወልድ ለማሻገር ትልቅ ዕድል መሆኑንና ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።


የዲፕሎማቲክ ልዑካን ቡድን አባላት የላሊበላ ጉብኝት የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ማንሰራራት የሚያረጋግጥ ነው ያሉት ደግሞ የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ መሳይ ወዳጆ ናቸው።

የመደመር መንግሥት ለቱሪዝም ዘርፍ የሰጠው ትኩረት የላሊበላን ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ቅርስ በመጠበቅ፣ በማልማትና በመንከባከብ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026