🔇Unmute
አሶሳ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአማራጭ ኢነርጂ ተደራሽነትን በማስፋፋት ማህበረሰቡን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት እንደሚጠናከሩ አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም አተገባበር ላይ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች ጋር በአሶሳ ከተማ መክሯል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ አስተማማኝ፣ ተመጣጣኝና ቀጣይነት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት የመሰረተ ልማት ግብ ብቻ ሳይሆን የዜጎችን ሕይወት ያቃልላል።
የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝ እና ተደራሽ ለማድረግ የኢነርጂ ፖሊሲ ወጥቶ ሥራ ላይ መዋሉን ገልፀው፣ ፖሊሲው የግሉን ዘርፍ የሚያበረታታ እና የኃይል ተደራሽነትን የሚያሳድግ መሆኑን አስረድተዋል።
ብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች የሶላር ኢነርጂ ተጠቃሚነትን የሚያሳድግ እና በደን ጭፍጨፋ በአካባቢ ላይ የሚደርስን ተፅዕኖ የሚቀንስ ነው ብለዋል።
አማራጭ የታዳሽ ኃይል ተደራሽነትን በማስፋፋት ህብረተሰቡን የሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ የኃይል መሠረተ ልማት ዝርጋታ እና አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ታሪኩ ኩመራ በበኩለቸው፤ በፕሮግራሙ በክልሉ የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎች በገጠሩ አካባቢ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ መምጣታቸውን እና ይህም በርካታ ዜጎችን ከድካም መታደጉን ተናግረዋል።
የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችን የሚያመርቱ ማህበራትን መደገፍ ዜጎች ማገዶ ፍለጋ የሚያባክኑትን ጊዜና ጉልበት ለመቀነስና የአየር ብክለትን ለመከላከል ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል።
ለሁለት ቀን በሚቆየው መድረክ በክልሉ በአነርጂ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ላይ ምክክር እንደሚደረግ ተመላክቷል።
ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...
Jul 19, 2026
ሐረር፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 47 አዳዲስ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን የክልሉ ኢን...
Jul 16, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የደብረ ማርቆስ ንጉሥተክለሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ የሕዝቡን የተዳፈነ የዘመናት የልማት ጥያቄ የመለሰ ነው ሲሉ የ...
Jul 14, 2026
ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መ...
Jul 11, 2026