የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር "ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት፤ መንገዳችን ኃላፊነታችን" በሚል መሪ ሃሳብ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩን በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል።


የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክብረ በዓሉ ስኬቶች በመዘከር የወደፊቱን ዘመናዊ የመንገድ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ግቦች የሚታደሱበት አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርም ባለፉት 75 ዓመታት ትውልድ ተሻጋሪ ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ከፍተኛ አቅም እየገነባ የመጣ ተቋም መሆኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይም ጥራታቸውን የጠበቁ፣ ዘላቂ፣ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የሚጣጣሙና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ያካተቱ የመንገድ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት ላይ ትኩረት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ የመንገድ መሠረተ ልማት እድገት የሕዝቡን ኢኮኖሚያዊ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነባ መሆኑንም አስረድተዋል።

የሕዝቦችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የመሠረተ ልማት ግንባታው በይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው ሚኒስቴሩም ለአስተዳደሩ የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የቦርድ ሰብሳቢ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ አስተዳደሩ በ75 ዓመታት ጉዞው የሀገሪቱ ልማት ዋነኛ ምሰሶ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የመንገድ ሽፋን ከ180 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ መድረሱን በመጠቆም፣ በቅርብ ዓመታት ብቻ ከ44 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ አዳዲስ መንገዶች በመገንባት የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ለማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።

የመንገድ መሠረተ ልማት ሕዝቦችን ከማቀራረብ ባለፈ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እድገት እያፋጠነ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን ናቸው።


የኢትዮጵያ የመንገድ አውታር መስፋፋት ተቋማዊ የቴክኖሎጂ አቅምን ከማሳደጉም በተጨማሪ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳ እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።

በመጨረሻም ለተቋሙ ስኬት መሠረት ለጣሉ የቀድሞ አመራሮች የመንገድ ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ አስተዋጽኦ ላበረከቱ መሐንዲሶች፣ ባለሙያዎችና ሠራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ 47 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደሥራ ገብተዋል

ሐረር፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 47 አዳዲስ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን የክልሉ ኢን...

Jul 15, 2026