🔇Unmute
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በበልግ እርሻ ተዘርተው የደረሱ ሰብሎችን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ የእንክብካቤና የክትትል ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ የክልሉ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በበልግ ወቅት በተለያዩ ሰብሎች የለሙ ማሳዎችን እየገበኙ ነው።
በጉብኝቱ ወቅት የቢሮው ኃላፊ መምሩ ሞኬ እንዳሉት፤ በሲዳማ ክልል በበልግ እርሻ ተዘርተው የደረሱ ሰብሎችን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በክልሉ በበልግ እርሻ በቆሎ፣ ቦሎቄና ሌሎች ሰብሎችን ጨምሮ 152 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ለምቷል ብለዋል፡፡
ከዚህም 24 ሚሊየን ኩንታል ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተው፤ በምርት የተሸፈነውን ማሳ ውጤታማ ለማድረግም የእንክብካቤና የክትትል ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል፡፡
በበልግ ወቅት የመስኖና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም የለማው ሰብል የሚጠበቀውን ምርት እንዲሰጥ እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026