የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት በከተማዋ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታን በለሚ ኩራ ከፍለ ከተማ ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፥ የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታው ወጣቶችን በክህሎት በማልማት የሀገርን እድገት ለማፋጠን ያለመ ነው ብለዋል።

ባለፉት የለውጥ አመታት በመዲናዋ ወጣቶች የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ላይ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል።


እነዚህ በክህሎትና በቴክኖሎጂ የበቁ ወጣቶች አሁን ላይ ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው በሀገር ሁለንተናዊ እድገት ላይ የበኩላቸውን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

አሁን ላይ ወጣቶችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ልክ የማብቃት ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።

አዲሱ ስማርት ፖሊቴክኒክ የጀርመንን የቴክኒክና ሙያ ልምድ መነሻ በማድረግ፣ በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚገነባና ትውልድ ተሻጋሪ እውቀት የሚገበይበት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል።

ኮሌጁ ወጣቶች እውቀትን የሚታጠቁበት፣አዕምሮ እና የሚሰሩ እጆች ተጣጥመው ሀሳብ የሚያፈልቁበት መሆኑን ገልጸዋል።

ኮሌጁ በአመት በርካታ አዳዲስ ሰልጣኞችን የመቀበል አቅም እንደሚኖረው ጠቁመው፤ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙኒኬሽንና በቴክስታይል ቴክኖሎጂ መስኮች ያሰለጥናል ብለዋል።


ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ፣ በጀትና ጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ በበኩላቸው፤ የሚገነባው ኮሌጅ ወጣቶች በስልጠና ወቅት የሚያመጧቸውን የቴክኖሎጂ ሀሳቦችና የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባራዊ ቢዝነስ እንዲቀይሩ፣የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱና ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026