🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት በከተማዋ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታን በለሚ ኩራ ከፍለ ከተማ ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፥ የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታው ወጣቶችን በክህሎት በማልማት የሀገርን እድገት ለማፋጠን ያለመ ነው ብለዋል።
ባለፉት የለውጥ አመታት በመዲናዋ ወጣቶች የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ላይ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል።

እነዚህ በክህሎትና በቴክኖሎጂ የበቁ ወጣቶች አሁን ላይ ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው በሀገር ሁለንተናዊ እድገት ላይ የበኩላቸውን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
አሁን ላይ ወጣቶችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ልክ የማብቃት ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።
አዲሱ ስማርት ፖሊቴክኒክ የጀርመንን የቴክኒክና ሙያ ልምድ መነሻ በማድረግ፣ በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚገነባና ትውልድ ተሻጋሪ እውቀት የሚገበይበት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል።
ኮሌጁ ወጣቶች እውቀትን የሚታጠቁበት፣አዕምሮ እና የሚሰሩ እጆች ተጣጥመው ሀሳብ የሚያፈልቁበት መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሌጁ በአመት በርካታ አዳዲስ ሰልጣኞችን የመቀበል አቅም እንደሚኖረው ጠቁመው፤ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙኒኬሽንና በቴክስታይል ቴክኖሎጂ መስኮች ያሰለጥናል ብለዋል።

ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ፣ በጀትና ጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ በበኩላቸው፤ የሚገነባው ኮሌጅ ወጣቶች በስልጠና ወቅት የሚያመጧቸውን የቴክኖሎጂ ሀሳቦችና የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባራዊ ቢዝነስ እንዲቀይሩ፣የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱና ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026