የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

Jul 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስፋፊያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ ማስተር ፕላኑ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ስርዓት ይበልጥ ዘመናዊ ፤አስተማማኝና በዲጂታል የተደገፈ ለማድረግ የተዘጋጀ ታሪካዊ ፍኖተ ካርታ ነው።


የአሰራር ስርዓቱ የምህንድስና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ቅድሚያ የሚሰጠው ሀገራዊ የልማት አጀንዳ መሆኑን አስረድተዋል።

በተጨማሪም ማስተር ፕላኑ ለኢትዮጵያ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትና የማህበራዊ ትራንስፎርሜሽን መሠረት እንደሚሆን ተናግረዋል።

በጥናቱ ሰነድ መሠረት፣የሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ከፍተኛ ፍላጎት በፈረንጆቹ 2025 ካለበት 4 ሺህ 289 ሜጋ ዋት በ2049 ወደ 39 ሺህ 327 ሜጋ ዋት ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ ዕድገት ከሕዝብ ቁጥር መጨመር፣ ከከተሞች መስፋፋት፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ከኢ-ሞቢሊቲ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ መሆኑም ተጠቅሷል።

ይህንን ፍላጎት ለማሟላት እስከ 2049 ድረስ በሀገር አቀፍ ደረጃ 128 አዳዲስ ሰብስቴሽኖችን መገንባት ያስፈልጋል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026