የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

Jul 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስፋፊያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ ማስተር ፕላኑ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ስርዓት ይበልጥ ዘመናዊ ፤አስተማማኝና በዲጂታል የተደገፈ ለማድረግ የተዘጋጀ ታሪካዊ ፍኖተ ካርታ ነው።


የአሰራር ስርዓቱ የምህንድስና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ቅድሚያ የሚሰጠው ሀገራዊ የልማት አጀንዳ መሆኑን አስረድተዋል።

በተጨማሪም ማስተር ፕላኑ ለኢትዮጵያ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትና የማህበራዊ ትራንስፎርሜሽን መሠረት እንደሚሆን ተናግረዋል።

በጥናቱ ሰነድ መሠረት፣የሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ከፍተኛ ፍላጎት በፈረንጆቹ 2025 ካለበት 4 ሺህ 289 ሜጋ ዋት በ2049 ወደ 39 ሺህ 327 ሜጋ ዋት ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ ዕድገት ከሕዝብ ቁጥር መጨመር፣ ከከተሞች መስፋፋት፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ከኢ-ሞቢሊቲ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ መሆኑም ተጠቅሷል።

ይህንን ፍላጎት ለማሟላት እስከ 2049 ድረስ በሀገር አቀፍ ደረጃ 128 አዳዲስ ሰብስቴሽኖችን መገንባት ያስፈልጋል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026