የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የ'ዌልመል' መስኖ ፕሮጀክት ግብርናውን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አቅም ፈጥሯል

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሎ መና ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ የ'ዌልመል' መስኖ ፕሮጀክት የግብርና ሥራን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አቅም የፈጠረ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሥራ ኃላፊዎችና የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ ለአካባቢው ማኅበረሰብ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን የ'ዌልመል' የመስኖ ፕሮጀክትን ጎብኝተዋል።


የመስኖ ፕሮጀክቱ የአካባቢውን አርሶና አርብቶ አደሮች ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

ፕሮጀክቱ በመንግሥት ትኩረት በበጀት ዓመቱ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃ ሲሆን፣ የአካባቢውን ማኅበረሰብ የመስኖ ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል።

በመስክ ምልከታው ላይ የተገኙት በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመስኖ ፕሮጀክቶች ፕሮግራም ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ሊካሳ እንዳሉት፣ በሀገሪቱ የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት የአርሶና አርብቶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።


በዚህም አርሶና አርብቶ አደሩ የተለያዩ የውኃ አማራጮችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መታየታቸውን አክለዋል።

በአርሶና አርብቶ አደሩ ማኅበረሰብ አካባቢ የዝናብ እጥረትና ድርቅ ለዜጎች ሕይወት ፈተና ሆኖ መቆየቱን የገለጹት አቶ አሸናፊ፤ በየአካባቢው ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተከናወኑ አማራጭ የመስኖ መሠረተ ልማቶች ግንባታ ኑሯቸውን እየለወጡ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

ለዚህም በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ የተገነባው የዌልመል የመስኖ ፕሮጀክት አንዱ ማሳያና ከዚህ በፊት በሴፍቲኔት መርሃ ግብር ሲረዱ የነበሩ አርሶና አርብቶ አደሮችን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በዓመት ሁለትና ሦስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን አመልክተዋል።

ፕሮጀክቱ ከ12 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የማልማት አቅም ያለውና ከ24 ሺህ በላይ አርሶና አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን አብራርተዋል።

የደሎ መና ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኡመር መሐመድ በበኩላቸው፣ በወረዳው ሰፊ ሊለማ የሚችል የእርሻ መሬት ቢኖርም ከዝናብ እጥረት የተነሳ የአካባቢው ማኅበረሰብ የሴፍቲኔት ተረጂ ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል።


በመንግሥት ትኩረት በዚህ ዓመት ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው የዌልመል መስኖ ፕሮጀክት አርሶና አርብቶ አደሩ በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ በማልማት ወደተሻለ የኑሮ ደረጃ እንዲሸጋገር እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።

የጎምጎማ ቀበሌ አርሶና አርብቶ አደሮች መካከል ኢስማኤል አማን በሰጡት አስተያየት፣ ቀደም ሲል እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች የአካባቢያቸው ነዋሪዎች በሴፍቲኔት መርሃ ግብር ታቅፈው ሲረዱ መቆየታቸውን ተናግረዋል።


የመስኖ ፕሮጀክቱ በመጠናቀቁ በ1 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ ገበያ ተኮር ምርቶችን በማልማት ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅትም እያለሙ ካሉት ነጭ ሽንኩርት 2 ሚሊዮን ብር ገቢ እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም የዝናብ ወቅትን ብቻ በመጠበቅ በዓመት አንድ ጊዜ ያመርቱ እንደነበርና ኑሯቸውም ከእጅ ወደ አፍ እንደነበር ያስታወሱት ደግሞ ሌላው የመስኖ ተጠቃሚ አደም በያን ናቸው።


አሁን ላይ በመስኖ ፕሮጀክቱ በመጠቀም ምርት በስፋት እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።


አቶ አብዱላሂ ጅብሪል በበኩላቸው፣ የዌልመል መስኖ ፕሮጀክት ከሴፍቲኔት ጠባቂነት አላቆን በራሳችን እንድንቆም አግዞናል፤ በመስኖው በመታገዝ ሰብል እንዲሁም ገበያ ተኮር አትክልትና ፍራፍሬዎችን በማምረት ተጠቃሚ ሆነናል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026