የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአፋር ክልልን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ ነው

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፣ጳጉሜን 1/2018(ኢዜአ) ፡-የአፋር ክልልን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኀላፊ ኡመር ኑር ገለጹ።

"የእመርታ ቀን" በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።


በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኀላፊ ኡመር ኑር ፤ የአፋር ክልል ብዙም ሳይለማ የቆየ ሰፊ መሬትና እምቅ የተፈጥሮ ሃብት ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ በተለይም በመስኖ ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት መኖሩን በማንሳት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የበጋ መስኖን ጨምሮ ሌሎችም የግብርና ልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።

የመሰኖ ስራዎችን በማጠናከር መሬት በተጠናከረ አቅም ወደ ምርት ለማስገባት በሚደረገው ጥረት በርካታ ወጣቶች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረት በተሳካ ሁኔታ መቀጠሉን ተናግረዋል።

የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ አኗኗር መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች በመጠናከር ተጠቃሚ ማድረግ በመቻሉ ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ጥሩ መሰረት እየያዘ መሆኑን ገልጸዋል።

የአፋር ክልልን ሰፊ መሬትና እምቅ የተፈጥሮ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።


የአፋር ክልል የፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ኀላፊ አብዱ መሐመድ፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት አፋር ክልልን የተለየ ገፅታ ያላበሱ ስኬታማ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

በተለይም በግብርና ፣ኢንዱስትሪ በማዕድንና አንሰሳት ልማት እመርታዊ ስኬት ስለመመዝገቡ ተናግረዋል።


በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በየደረጃው ያሉ የክልሉ አመራሮችና የሠመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026