የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ እመርታዊ ውጤቶችን እያስመዘገበች ወደ ላቀ ብልፅግና እየተጓዘች ትገኛለች-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እያመረተች በርካታ እመርታዊ ውጤቶችን እያስመዘገበች ወደ ላቀ ብልፅግና እየተጓዘች ትገኛለች ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች የጀመረችውን ሁለንተናዊ የለውጥና የብልፅግና ጉዞ በማጠናከር ከተረጅነት ወደ አምራችነት በጽኑ መሸጋገር ላይ እንደምትገኝም ተናግረዋል።

ዛሬ ጳጉሜን 1 ቀን 2018 ዓ.ም "እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል "የእመርታ ቀን" በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።


በመርሐ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአጋር ድርጅቶች እና የግሉ ዘርፍ ተወካዮች ተገኝተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ ባለፉት ዓመታት የተተገበሩት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና የፋይናንስ ሥርዓት ማዘመኛ እርምጃዎች የኢኮኖሚውን መሠረት ማጠናከራቸውን ገልጸዋል።

በተለይም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

በዚህም በሥጋ፣ በሩዝ፣ በበቆሎ፣ በወተት እና በሌሎችም ሰብሎች በሌማት ትሩፋትና በክላስተር እርሻ አማካኝነት የተመዘገቡት ስኬቶች የኢትዮጵያን ምግብ የማምረት አቅም ማሳደጋቸውን ገልጸዋል።

በማኑፋክቸሪንግና አግሮ ኢንዱስትሪ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄና በኢንዱስትሪ ፓርኮች አማካኝነት የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ኢትዮጵያን ከሸማችነት ወደ አምራችነትና ተወዳዳሪነት መዋቅራዊ ሽግግር ማድረጓን ተናግረዋል።

በማዕድን ዘርፍ የተፈጥሮ ሀብትን በእሴት ጭማሪ ወደ ከፍተኛ ኢኮኖሚ በመለወጥ አዳዲስ የኤክስፖርት ዕድሎች መፈጠራቸውን አብራርተዋል።

በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ የኢ-ፋይሊንግ፣ የኢ-ፔይመንት እና የአሠራር ዲጂታላይዜሽን ግልጽነትና ቅልጥፍናን በማምጣት የታክስ ሕግ ተገዥነትን ማጠናከራቸውን ጠቁመዋል።

አምራችነት እሳቤ፣ ስልት እና ግብ መሆን እንዳለበት ያሰመሩበት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ማናቸውም ሥራ እና ፕሮጀክት እሴት ካልጨመረና ምርት ካላተረፈረፈ ብክነት እንደሆነ ገልጸዋል።


የአገልግሎት አሰጣጥን ከእጅ መንሻና ከሙስና ነጻ ለማድረግ አሠራሮችን ወደ ዲጂታል ማሸጋገር እንደሚገባም አሳስበዋል።

ኢትዮጵያ እየተለወጠች፣ እያንሰራራች፣ እያመረተች ወደ ላቀ ብልጽግና እየተጓዘች እንዳለች ተናግረው፤ ለዚህ የኢትዮጵያ ከፍታ በተሰማሩበት ዘርፍ ሌሊትና ቀን ለደከሙ ኢትዮጵያውያን፣ የኢትዮጵያ ወዳጆች እና አጋሮች ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026