የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በእንስሳት ሀብት ልማት ዘርፍ እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፦በእንስሳት ሀብት ልማት ዘርፍ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት እመርታዊ ለውጥ መመዝገቡን የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ተዋፅዖ ምርታማነትን መጨመር ማስቻሉንም ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት በብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፍ ትኩረት ከተሰጣቸው መካከል በግብርናው ዘርፍ የእንስሳት ሃብትና ተዋፅዖ ምርትና ምርታማነት ላይ በተከናወኑ ተግባራት ውጤታ ማስመዝገብ ተችሏል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ በተደረገው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርም የወተት፣ ዶሮ፣ እንቁላልና ሥጋ፣ በዓሳና በንብ ማርባት ብሎም ማር ምርት ላይ ለውጥ ተመዝግቧል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አስራት (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከእንስሳት ሀብት የሚፈለገውን ጥቅም ለማግኘት ባለፉት ዓመታት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ሲከናወን በመቆየቱ እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል፡፡

በተለይም በሥጋ ወጪ ንግድ እንዲሁም በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከፍተኛ ስኬት እና ምርታማነት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡

በተለይም የተቀናበሩና ጥራታቸው የተጠበቀ ሥጋና የሥጋ ውጤቶችን ወደ ውጭ በመላክ በኩል ከታቀደው በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸው፤ ይህም የዘርፉን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ አዎንታዊ እርምጃ መሆኑን ጠቁመዋል።

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በወተት፣ በዶሮ እንቁላልና ሥጋ፣ በአሳ እንዲሁም በንብ ማር ምርታማነት ላይ ጉልህ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል፡፡

ይህ ስኬት የሴቶችና የወጣቶችን የሥራ ዕድል ከማስፋት ባለፈ፣ በቤተሰብ ደረጃ የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።

በሌማት ትሩፋት፣ በወጪ ንግድ እና በተለይም በእንስሳት ዘርፍ የተመዘገቡት ድሎችና አዎንታዊ ውጤቶች ለቀጣይ ሥራዎች እንደ መስፈንጠሪያ ሆነው እንደሚያገለግሉ ገልጸዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የተገኙት ስኬቶች የዘርፉን እመርታ ያሳደጉ መሆናቸውን አመልክተው፤ በቀጣይ ሂደት በከፍተኛ ቁርጠኝነትና በላቀ ሞራል ለመስራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አስረድተዋል።

ዘንድሮ የተመዘገበውን የምርታማነት መነሻ በማድረግና የተገኙትን ድሎች በማሳደግ የላቀ የምርት ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026