🔇Unmute
ወልቂጤ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ ለአዲስ ዓመት የበዓል ገበያ የኢንዱስትሪና ግብርና ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በተለያዩ አማራጮች መቅረባቸውን በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ።
በጳጉሜን ወር እለቶቹን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከማክበር በተጓዳኝ ኢትዮጵያዊያን አዲስ ዓመትን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ይገኛሉ።
በዚሁ መሰረትም የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች፣ የእርድ እንስሳት፣ አልባሳትና ሌሎችንም በመሸመት አዲሱን ዓመት ለመቀበል እየተዘጋጁ ነው።

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወልቂጤ ከተማና አካባቢው የበዓል ግብይትና አቅርቦቱን በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር ቅኝት በማድረግ የሚመለከታቸውን የስራ ሃላፊዎችና ሸማቾችን አነጋግሯል።
የወልቂጤ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ንቅበሸዋ፤ ለበዓል የምርቶችና የእርድ እንስሳት አቅርቦት በበቂ ሆኔታ መኖሩን ገልጸዋል።
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንዲሁም ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ቀደም ብሎ በቅርበት በመነጋገር ለበዓል ገበያ ዝግጅት መደረጉን አንስተው በዚህም በተመጣጣኝ ዋጋ በቂ አቅርቦት እንዲኖር ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
የቅዳሜ እና እሁድ ገበያን ጨምሮ በተለያዩ የገበያ አማራጮች በብዛትና በተለያዩ አማራጮች መቅረቡን አንስተው ህገ ወጥ ግብይትና ያልተጋባ ዋጋ ጭማሬ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን የወልቂጤ ቅርንጫፍ ተጠሪ ናትናኤል ደበበ፤ ከእርሻ አርሶ አደሮች በቀጥታ በሚያመጡት ምርት፤ ከፋብሪካ እና ከቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ምርቶች በብዛትና በጥራት ለሸማቾች መቅረቡን ተናግረዋል።
ለበዓል ሲሸምቱ ካገኘናቸው መካከል አቶ ጥበበ ታምሩ፣ ወይዘሮ አመለወርቅ ታደሰ እና ወይዘሮ ብርዝነሽ አረጋ፤ የበዓል ገበያ አቅርቦቱ ብዙ አማራጮች ያሉት በመሆኑ በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026