የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በወልቂጤ ከተማ ለበዓል ገበያ የኢንዱስትሪና ግብርና ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በተለያዩ አማራጮች ቀርበዋል

Sep 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ ለአዲስ ዓመት የበዓል ገበያ የኢንዱስትሪና ግብርና ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በተለያዩ አማራጮች መቅረባቸውን በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ።

በጳጉሜን ወር እለቶቹን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከማክበር በተጓዳኝ ኢትዮጵያዊያን አዲስ ዓመትን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ይገኛሉ።

በዚሁ መሰረትም የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች፣ የእርድ እንስሳት፣ አልባሳትና ሌሎችንም በመሸመት አዲሱን ዓመት ለመቀበል እየተዘጋጁ ነው።


በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወልቂጤ ከተማና አካባቢው የበዓል ግብይትና አቅርቦቱን በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር ቅኝት በማድረግ የሚመለከታቸውን የስራ ሃላፊዎችና ሸማቾችን አነጋግሯል።

የወልቂጤ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ንቅበሸዋ፤ ለበዓል የምርቶችና የእርድ እንስሳት አቅርቦት በበቂ ሆኔታ መኖሩን ገልጸዋል።

ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንዲሁም ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ቀደም ብሎ በቅርበት በመነጋገር ለበዓል ገበያ ዝግጅት መደረጉን አንስተው በዚህም በተመጣጣኝ ዋጋ በቂ አቅርቦት እንዲኖር ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

የቅዳሜ እና እሁድ ገበያን ጨምሮ በተለያዩ የገበያ አማራጮች በብዛትና በተለያዩ አማራጮች መቅረቡን አንስተው ህገ ወጥ ግብይትና ያልተጋባ ዋጋ ጭማሬ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።


በኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን የወልቂጤ ቅርንጫፍ ተጠሪ ናትናኤል ደበበ፤ ከእርሻ አርሶ አደሮች በቀጥታ በሚያመጡት ምርት፤ ከፋብሪካ እና ከቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ምርቶች በብዛትና በጥራት ለሸማቾች መቅረቡን ተናግረዋል።

ለበዓል ሲሸምቱ ካገኘናቸው መካከል አቶ ጥበበ ታምሩ፣ ወይዘሮ አመለወርቅ ታደሰ እና ወይዘሮ ብርዝነሽ አረጋ፤ የበዓል ገበያ አቅርቦቱ ብዙ አማራጮች ያሉት በመሆኑ በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026