የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>በሰሜን ወሎ ዞን በጋዞ ወረዳ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመረቁ</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ የካቲት 09/2017 (ኢዜአ) በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ጋዞ ወረዳ በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ።

ከተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች ውስጥም የአስተዳደር ምክር ቤት ህንፃን ጨምሮ ሶስት ጤና ጣቢያዎች፣ ስምንት የትምህርት ቤት ማሻሻያና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ይገኝበታል።

በተጨማሪም ሰባት ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ፣ አነስተኛ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት፣ የመስኖ ካናል ፣ ሁለት የእንስሳት ጤና ኬላና የእንስሳት ዝርያ ብዜት ማዕከላትና ሌሎችም ይገኙበታል።

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በምረቃ ስነ-ስርዓ ላይ እንደገለጹት የተገነቡት የልማት ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ናቸው።


ፕሮጀክቶቹን ጠብቆ ለረጅም ጊዜ ለመጠቀምና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር የልማት መሠረት የሆነውን ሠላም ማጽናት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው የተመረቁትና በጉብኝት የታዩት የልማት ፕሮጀክቶች በአመራሩና በህዝቡ ቁርጠኝነት የተከናወኑ ናቸው ብለዋል።

አሁንም ሠላምን ይበልጥ በማጽናት የህዝብን ተጠቃሚነት በምናረጋግጥበት ልማት ላይ ይበልጥ መስራት ይገባል ሲሉም አክለዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አራጌ ይመር በበኩላቸው በዞኑ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በቀጣይም አሁን የሚታየውን የተሻለ ሠላም ይበልጥ በዘላቂነት በማረጋገጥ የዞናችንን ልማት ለማፋጠን በቁርጠኝነት ከህብረተሰቡ ጋር በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

በምረቃ ስነ- ስርዓቱ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የአመራር አባላት እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026