የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

Jun 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ገለጹ።

የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ መርሃ ግብር በዲጂታል ሳይንስ ዘርፎች እንደ አንድሮይድ ማበልጸግ፣ ዳታ አናሊቲክስ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዌብ ዲዛይን መሰረታዊ ስልጠናዎችን ያካተተ ነው።

የመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማና ግብ አምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በዲጂታል ክህሎት በማብቃት፣ ሀገሪቱ በዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ያላትን ተወዳዳሪነት ማረጋገጥ ነው።

ይህም ለወጣቶች ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያለው ሰርቲፊኬት እና የስራ ዕድሎችን በመፍጠር በኩል ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎቹ እንደገለጹት ከመደበኛው ትምህርት በተጨማሪ ራሳቸውን ከዲጂታሉ ዓለም ጋር ለማላመድ ጥረት እያደረጉ ነው።

በለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው አቢጊያ ዳንኤል፣ ወደፊት የሶፍትዌር ኢንጂነር የመሆን ህልሟን ለማሳካት በትምህርት ቤትና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመቻቹ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድሎችን እየተጠቀመች መሆኗን ገልጻለች።

በዚሁ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አላዛር ማስሬ፣ በዲጂታል ዘርፍ ራሱን እያበቃ መሆኑን ገልጾ፤ ትውልዱ ነገ ተወዳዳሪ ዜጋ ለመሆን ራሱን ከቴክኖሎጂ ጋር ማላመድ የግድ መሆኑን ተናግሯል።

በድልበር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አቤል ሙሉጌታ በበኩሉ፣ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መውሰዱን ገልጾ፣ ተማሪዎች ከቴክኖሎጂ ጋር ለመራመድ የተፈጠረውን መልካም አጋጣሚ እንዲጠቀሙበት መክሯል።

የዌብ ዲዛይን ስልጠና መውሰዱንና ይህም በዘርፉ ያለውን መሰረታዊ እውቀት እንዳስጨበጠው የተናገረው ደግሞ ተማሪ ፍራኦል ተሾመ ነው።


የለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ሰለሞን ዲሮ ትምህርት ቤቱ ከተለያዩ አካላት ጋር በመተባበር በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና በሌሎች የቴክኖሎጂ ዘርፎች ለተማሪዎች ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


የድልበር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ተመስገን ቶሊና በበኩላቸው፣ ተማሪዎችና መምህራን የ5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ትምህርት ቤቱ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026