የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

Jul 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ።

የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ በአዳማ ገልማ ጨፌ እየተካሄደ ይገኛል።


ፕሬዚዳንቱ የክልሉን መንግሥት የዕቅድ አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት፣ በበጀት ዓመቱ ሰላምን ከማጽናትና መልካም አስተዳደርን ከማስፈን ጎን ለጎን ለልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት በ2018 ዓ.ም በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

ግብርና የኢኮኖሚ ዕድገት ዋና ምሰሶ በመሆኑ እየተከናወነ ባለው ሥራ ትላልቅ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፣ ይህም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር እየተደረገ ባለው ጥረት ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

በ2017/18 የምርት ዘመን በነበረው የመኸር ግብርና ሥራ 11 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለምቶ የተሻለ ምርት ማግኘት ተችሏል ብለዋል።

በ2018/19 የምርት ዘመን የመኸር ግብርና ልማት 12 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ሰብሎች ይለማሉ ብለዋል።

እስከ አሁን ባለው ሂደትም 9 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ታርሶ ለዘር የተዘጋጀ ሲሆን፣ 5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው ደግሞ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ተሸፍኗል ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ ከሻይ ቅጠል ልማት ጋር ተያይዞ ከዚህ ቀደም የተተከሉትን ከመንከባከብ ባለፈ፣ ዘንድሮ ልማቱን ለማጠናከር በተደረገ ጥረት እስካሁን ድረስ 17 ነጥብ 9 ሚሊዮን ችግኝ መተከሉን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም ሥራው ቀጣይነት ባለው መልኩ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራም በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም እርከኖች፣ የውሃ ማስተላለፊያ መዋቅሮች፣ ልዩ ልዩ ዓይነት እርጥበትን መጠበቂያ መዋቅሮች እንዲሁም መሬትን ከሰውንና ከእንስሳት ንክኪ የመከላከል ሥራ መሠራቱን አመልክተዋል፡፡

በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በኩልም የአቮካዶ፣ የሙዝ፣ የፓፓያ፣ የአፕል እና የሌሎች የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መተከላቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026