
አዲስ አበባ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአፍሪካ ድምፅ ለመሆን እየሰራችው ያለው ስራ የሚደነቅ ነው ሲሉ የኢጋድ ስራ አስፈፃሚ ቃል አቀባይ ፓቲያንስ ኒያንግ ገለጹ።
በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን የኢጋድ ስራ አስፈፃሚ ቃል አቀባይ ፓቲያንስ ኒያንግ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸው ወቅት በተመለከቱት ጉዳይ አስተያየታቸውን የሰጡት ቃል አቀባዩዋ ኢዜአ አፍሪካን ያማከለ አካሄድን እየተከተለ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።
የአፍሪካን አመለካከት በማስተዋወቅ እና በሚዲያ ዘርፍ ላይ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማምጣት እያደረገ ያለውን ጥረትም አድንቀዋል።
ኢዜአ አፍሪካ ላይ ያተኮረ የሚዲያ ተቋም ሆኖ የማገልገል ዓላማ ያለው ፐልስ ኦፍ አፍሪካ የተሰኘ አህጉር አቀፍ የሚዲያ መድረክ በማቋቋም ላይ ይገኛል።
ጉብኝታቸውን ተከትሎ ቃል አቀባዩዋ ኢትዮጵያ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ በሚል የጀመረችው የዲጂታል ሚዲያ አማራጭ ለአፍሪካ ዲጂታል እድገት ጥሩ ምሳሌ እንደሚያደርጋት ተናግረዋል።
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ የተሰኘው ዲጂታል ሚዲያም የአፍሪካን ታሪክ ለመንገር የበኩሉን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።
አፍሪካውያን በዓለም ዙሪያ እየተከሰተ ባለው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ፈጠራ ላይ የበለጠ ኢንቨስት እያደረጉ ነው፣ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ እኛም ወደ ኋላ እንዳልቀረን ያመላክታል ብለዋል።
እንደ ቃል አቀባዩዋ ገለጻ፣ አፍሪካ የአህጉሪቱን እውነተኛ ታሪኮች ለመንገር በምታደርገው ጥረት ፐልስ ኦፍ አፍሪካ የራሱን ሚና እንደሚጫወት ገልጸው፣ እኛ የአፍሪካ መፍትሄዎች ከአፍሪካዊ መፍትሄዎች ይመነጫሉ እንላለን ነው ያሉት።
ለእርሳቸው አፍሪካ በራሷ እና በአካባቢያዊ እይታዎች ማስተዋወቅ ያለባት ውብ ታሪኮች ያሏት ውብ አህጉር ነች ሲሉም ገልጸዋል።
ኢጋድ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና ከሌሎች የኢጋድ ክልል ሚዲያዎች ጋር በተለያዩ መንገዶች ተባብሮ ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።
ከተቀሩት የሚዲያ ተቋማት ጋር በመተባበር በቀጣናው የሚሰሩ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን አቅም ለመገንባት ኢጋድ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
በዚህም ኢጋድ ቀደም ሲል ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረውን የአቅም ግንባታ ስልጠና አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለጋዜጠኞች እውቅና የመስጠት ስራን እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026