የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ኢትዮጵያ የአፍሪካ ድምፅ ለመሆን እየሰራችው ያለው ስራ የሚደነቅ ነው - የኢጋድ ቃል አቀባይ ፓቲያንስ ኒያንግ</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአፍሪካ ድምፅ ለመሆን እየሰራችው ያለው ስራ የሚደነቅ ነው ሲሉ የኢጋድ ስራ አስፈፃሚ ቃል አቀባይ ፓቲያንስ ኒያንግ ገለጹ።

በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን የኢጋድ ስራ አስፈፃሚ ቃል አቀባይ ፓቲያንስ ኒያንግ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸው ወቅት በተመለከቱት ጉዳይ አስተያየታቸውን የሰጡት ቃል አቀባዩዋ ኢዜአ አፍሪካን ያማከለ አካሄድን እየተከተለ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።

የአፍሪካን አመለካከት በማስተዋወቅ እና በሚዲያ ዘርፍ ላይ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማምጣት እያደረገ ያለውን ጥረትም አድንቀዋል።

ኢዜአ አፍሪካ ላይ ያተኮረ የሚዲያ ተቋም ሆኖ የማገልገል ዓላማ ያለው ፐልስ ኦፍ አፍሪካ የተሰኘ አህጉር አቀፍ የሚዲያ መድረክ በማቋቋም ላይ ይገኛል።

ጉብኝታቸውን ተከትሎ ቃል አቀባዩዋ ኢትዮጵያ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ በሚል የጀመረችው የዲጂታል ሚዲያ አማራጭ ለአፍሪካ ዲጂታል እድገት ጥሩ ምሳሌ እንደሚያደርጋት ተናግረዋል።

ፐልስ ኦፍ አፍሪካ የተሰኘው ዲጂታል ሚዲያም የአፍሪካን ታሪክ ለመንገር የበኩሉን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።

አፍሪካውያን በዓለም ዙሪያ እየተከሰተ ባለው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ፈጠራ ላይ የበለጠ ኢንቨስት እያደረጉ ነው፣ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ እኛም ወደ ኋላ እንዳልቀረን ያመላክታል ብለዋል።

እንደ ቃል አቀባዩዋ ገለጻ፣ አፍሪካ የአህጉሪቱን እውነተኛ ታሪኮች ለመንገር በምታደርገው ጥረት ፐልስ ኦፍ አፍሪካ የራሱን ሚና እንደሚጫወት ገልጸው፣ እኛ የአፍሪካ መፍትሄዎች ከአፍሪካዊ መፍትሄዎች ይመነጫሉ እንላለን ነው ያሉት።

ለእርሳቸው አፍሪካ በራሷ እና በአካባቢያዊ እይታዎች ማስተዋወቅ ያለባት ውብ ታሪኮች ያሏት ውብ አህጉር ነች ሲሉም ገልጸዋል።

ኢጋድ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና ከሌሎች የኢጋድ ክልል ሚዲያዎች ጋር በተለያዩ መንገዶች ተባብሮ ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።

ከተቀሩት የሚዲያ ተቋማት ጋር በመተባበር በቀጣናው የሚሰሩ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን አቅም ለመገንባት ኢጋድ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

በዚህም ኢጋድ ቀደም ሲል ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረውን የአቅም ግንባታ ስልጠና አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለጋዜጠኞች እውቅና የመስጠት ስራን እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026