የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>አየር መንገዱ አህጉራዊ የካርጎ አገልግሎት ሽልማቶችን አገኘ</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በአፍሪካ ቀዳሚ በመሆን ሁለት ሽልማቶችን ማግኘቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ አስታወቀ።

“Aviation Achievement Awards” የተሰኘ የአቪዬሽን ዘርፍ የሽልማት መርሃ ግብር በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ዱባይ ተከናውኗል።


የኢትዮጵያ ካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት የህክምና ቁሳቁሶችን በማጓጓዝ እና አጠቃላይ በካርጎ አገልግሎት ዘርፎች ከአፍሪካ ቀዳሚ በመሆን ሽልማቶችን ማግኘቱን የአየር መንገዱ መረጃ ያመለክታል።

የአፍሪካ ምርጥ የፋርማ እቃ ጭነት አገልግሎት አየር መንገድ (Air Cargo Pharma Service of the Year,Africa) እና የአፍሪካ ምርጥ የዕቃ ጭነት አገልግሎት አየር መንገድ (Cargo Airline of the Year,Africa) ያገኛቸው ሽልማቶች ናቸው።

ሽልማቶቹ አየር መንገዱ ለልህቀት፣ ፈጠራ እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለደንበኞች ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላክቱ ናቸው።

ዓለም አቀፍ የዕቃ ጭነት በረራ አድማስ በማስፋት በዓለም ደረጃ ያለውን ተፎካካሪነት አጠናክሮ እንዲቀጥል አበርክቶ እንዳለውም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት መዳረሻዎቹንና አገልግሎቶቹን በማስፋፋት የመሪነት ሚናውን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አየር መንገዱ በመረጃው አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.