የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ ለመኸር እርሻ ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ ነው

Apr 22, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ በትግራይ ክልል ለመኸር እርሻ ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ በ2017/18 የምርት ዘመን የኩታ ገጠም አስተራረስ እና የእርሻ ሜካናይዜሽንን የማጎልበት ተግባር ትኩረት እንደተሰጠው ተገልጿል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አበራ ከደነው፤ በተያዘው የመኸር ወቅት ለአርሶ አደሩ የሚያስፈልገውን የምርጥ ዘር እና ሌሎች የግብአት አቅርቦት ሟሟላት የሚያስችሉ ተግባራት ቀደም ብለው መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት ባለፈው የምርት ዘመን በአርሶ አደሩ እና በምርምር ተቋማት ከተባዙት የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ምርጥ ዘር የመሰብሰብ እቅድ ተይዞ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

ከኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን እና ከህብረት ስራ ማህበራት ዩኒየኖች ጋር በመተባበር ለምርት ዘመኑ የሚሆን ከ100ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለማቅረብ ታቅዶ አሁን በስርጭት ላይ ይገኛል ብለዋል።


በክልሉ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ በኩታ ገጠም/ክላስተር/ እርሻ የስንዴ፣ የማሽላ፣ የጤፍና የሰሊጥ እና ሌሎች ምርቶችን ለማልማት 250ሺህ ሄክታር መሬት መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።

ከ130ሺህ ሄክታር የሚበልጠውን መሬትም በትራክተሮች በሜካናይዜሽን ማልማት የሚያስችል የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።

በጊዜያዊ አስተዳደሩ የክልሉ እርሻ ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ተክላይ አበበ(ዶ/ር)፤ የምርጥ ዘር አቅርቦትን ለማሳለጥ በ947 ሄክታር መሬት ላይ የምርጥ ዘር ብዜት ስራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

በዚህም መሰረት በመጪው ክረምት ከ800 በላይ ኩንታል የመስራችና ቅድመ መስራች ምርጥ ዘር ለማከፋፈል መታቀዱን ገልፀዋል።

በአክሱም ከተማ የሚገኘው የምዕባለ የምርጥ ዘር ማባዛትና ግብይት ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ ግሩም ገብረሰላማ በበኩላቸው ዩኒየኑ ግብርናን ለማዘመንና ምርትን በጥራትና በመጠን ለማሳደግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

ዩኒየኑ ከምርምር ማዕከላት የሚወጣን ምርጥ ዘር የማባዛትና የማከፋፈል ስራ በማከናወን የግብርና ግብዓቶችን ለሟሟላት ጥረት እያደረገ መሆኑና ለመኸር ወቅትም 7ሺህ 400 ኩንታል ምርጥ ዘር ለማከፋፈል ማቀዱን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026