
ዱራሜ ፡ ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፡- በከምባታ ዞን የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በአካባቢያቸው ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ እድልን እንደፈጠረላቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የዞኑ አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡
በከምባታ ዞን ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ጆሬ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ደሳለኝ ሎዴቦ ለኢዜአ እንደገለፁት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በእጃችን ያሉ ሀብቶችና ጸጋዎችን በአግባቡ አውቀን የተሻለ ተጠቃሚ እንድንሆን እያስቻለን ነው።
ከዚህ ቀደም የወተት ላም የማርባት ልምዱ ቢኖራቸውም ውጤታማ እንዳልነበሩ አንስተው በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ የነበሯቸውን የወተት ላሞች በተሻሻሉ የወተት ዝርያዎች በመቀየር ወደ እርባታ ገብተው የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል።

120 አርሶ አደር አባላት በወተት መንደር በመደራጀት በተቀናጀ መንገድ ወተት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል፡፡
ሌላኛው አርሶ አደር ወርቁ ወልዴ በበኩላቸው መርሃ ግብሩ አርሶ አደሩ ባለው የመሬት መጠን በርካታ ተግባራትን እንዲያከናውን እድልን የፈጠረ ነው ብለዋል፡፡

በመንደሩ ከሚገኙ አርሶ አደሮች ጋር በመደራጀት ከእርሻ ስራ በተጓዳኝ ዶሮ በማርባት እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡
በዚህም እያገኙት ያለው ገቢ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ ልጆቻቸውን በተገቢው መንገድ ከማስተማር በተጨማሪ ራሳቸውን በቁጠባ በማጠናከር ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ገልፀዋል፡፡

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ እንደገለፁት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራ ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት የሚያስችል የወተትና የዶሮ እንዲሁም የንብ መንደር በመፍጠር በርካታ ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራ ውስን መሬትን ለዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዲውል የማድረግ ስራ መሰራቱን ተናግሯል፡፡
በዚህም መርሃ ግብሩ የማህበረሰቡን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ተጠቃሚነትን በማሳደግ ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡

በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ አርሶ አደሮች በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር ተሳታፊ በመሆን እያስመዘገቡት የሚገኘው ውጤት ተስፋ ሰጪ መሆኑንም ዋና አስተዳዳሪው አክለዋል፡፡
በቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ጆሬ ቀበሌ በአንድ መንደር የተደራጁ 120 አርሶ አደሮች ላይ እየታየ ያለውን ዓይነት ለውጥ ለማስፋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026