የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአፍሪካ ሀገራት በምግብ ራስን የመቻል ራዕይን ለማሳካት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ሚያዚያ 28/2017 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ሀገራት የአህጉሪቷን በምግብ ራስን የመቻል ራዕይን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባቸው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ።

የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዴፕ) የ10 ዓመት ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ማድረጊያ ስነ ስርዓት ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ መካሄድ ጀምሯል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ በአፍሪካ ለምለም መሬት ላይ የተስፋ ዘር ተዘርቷል፤ ዘሩም ሙሉ ፍሬ እንዲሰጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በካዴፕ የትግበራ ጉዞ ውስጥ ከማፑቶ ድንጋጌ ተነስቶ ወደ ማላቦ አሁን ደግሞ የካምፓላ ድንጋጌ ላይ መድረሱን አመልክተዋል።

በአፍሪካ የግብርና ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል ተብሎ የታመነበት አዲሱ ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2036 እንደሚተገበር ጠቁመዋል።

የአፍሪካ ሀገራት በግብርናው ዘርፍ የሚያስመሰግን ለውጥ ቢያመጡም የካዴፕን ግቦችን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት አለመቻላቸውን ተናግረዋል።

የበጀት እጥረት፣ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ ማነስ፣ መሰረተ ልማቶች በበቂ ሁኔታ አለሟላት እና ሌሎች ፈተናዎች የፕሮግራሙ ውጤታማነት ላይ ተጽእኖ እንዳሳደሩ ነው ኮሚሽነሩ የገለጹት።

አፍሪካ መሬት ፣ ውሃ እና የቴክኒክ አቅሞች እያሏት በዓመት ከ50 እስከ 100 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በማድረግ ምግብ ከውጭ እንደሚያገቡ ጠቁመዋል።

ኮሚሽነር ቪላካቲ ይህን ያህል ከፍተኛ ወጪ ለምንድነው የምናወጣው? ብለን ራሳችንን በመጠየቅ ምርታማነታችንን ማሳደግ ላይ በትጋት መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

አዲሱ የካዴፕ ስትራቴጂ በምግብ ስርዓት ውስጥ በማምረት፣ በማቀነባበር፣ በማሰራጨት እና በመጠቀም ያለውን ሁሉን አቀፍ ሂደት የመቀየር ግብ ያለው መሆኑን አመልክተዋል።

የአፍሪካ ሀገራት ስትራቴጂውን በብሔራዊ እቅዶቻቸው በማካተት በሙሉ አቅም እና ቁርጠኝነት እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም ለግብርናው ዘርፍ አስፈላጊውን በጀት በመመደብ እና ሀብት በማሰባሰብ ለውጤታማነቱ እንዲሰሩ ጠይቀዋል።

ካዴፕን በሙሉ አቅም ከተገብርን በአፍሪካ ላሉ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች አጥጋቢ ምላሽ መስጠት ይቻላል ነው ያሉት ኮሚሽነሩ።

የአፍሪካ ሀገራት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ሳይታክቱ በመስራት እና ራስን ለለውጥ በማዘጋጀት ለአፍሪካ የተስፋ እና የብልጽግና ጮራ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የልማት አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ (አውዳ-ኔፓድ) ዋና ስራ አስፈጻሚ ናርዶስ በቀለ በበኩላቸው የአፍሪካ ሀገራት ለማሳደግ እና ለመለወጥ የግብርና አቅማቸውን በሚገባ መጠቀም እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026