የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የኮደርስ ስልጠናን እንዲወስዱ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው - የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠናን እንዲወስዱ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ መሆኑን የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገለፀ።

የ“አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ መርኃ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገ ሲሆን በኢትዮጵያ እና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥታት ትብብር እየተተገበረ ይገኛል።

ፕሮጀክቱ "ትውልድ ይማር፣ ትውልድ ይሰልጥን፣ ከዓለም ጋር ይፎካከር" በሚል እሳቤ ወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማዳበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ብቁ ማድረግ የሚያስችል ነው።

መርኃ ግብሩ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስ እና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት የሚያስጨብጥ ነው።


የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሮኒክስ ትምህርት ክፍል ዳይሬክተር መኮንን አበበ(ዶ/ር) የአምስት ሚሊየን ኮደርስ መርኃ ግብር ዜጎችን ከአለም ቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳስር ነው ብለዋል።

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እና ማህበረሰብ ስልጠናውን እንዲከታተሉ ለማድረግ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው በዚህም ስልጠናውን የተከታተሉ ተማሪዎችና ሰራተኞች ቁጥር ከ2ሺህ 800 መሻገሩን ተናግረዋል።

እስካሁን ባለው ሂደት 68 መምህራንና ከ730 በላይ የአስተዳደር ሰራተኞች ስልጠናውን ማጠናቀቃቸውንም ጠቅሰዋል።

የኮደርስ ስልጠና የተማሪዎችን የዲጂታል ክህሎት የሚያሳድግ መሆኑን ተከትሎ ስልጠናውን በስፋት እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም 1ሺህ 80 የመጀመሪያ አመት እንዲሁም ከሁለተኛ አመት በላይ ያሉ 983 ተማሪዎች ስልጠናውን ማጠናቀቃቸውን አብራርተዋል።

የኮደርስ ስልጠና የዲጂታል ክህሎትንና ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ በመሆኑ ሁሉም ስልጠናውን ቢከታተል ተጠቃሚ እንደሚሆንም አስገንዝበዋል።


በዩኒቨርሲቲው የኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ምህንድስና ተማሪ ሰለሞን ታረቀኝ የኮደርስ ስልጠና ለትምህርቱ እገዛ እንደሚያደርግለት ገልጿል።


ሌላው የኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ምህንድስና ተማሪ ቅዱስ ማሞ የኮደርስ ስልጠናን መውሰዱ በተለይ የጥናት ስራን ለማካሄድ እንደሚጠቅመው ተናግሯል።

ስልጠናው የዲጂታል ክህሎትን የሚያሳድግ በመሆኑ ሁሉም ተማሪ የተመቻቸውን ዕድል በመጠቀም ሊከታተለው እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025